2023-07-15 17:17:27
በአዲስ አበባ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶች በጀምላ እየታፈሱ መሆኑ ተሰማ
ወጣቶች በጀምላ የታፈሱት በአዲስአበባ ልዩ ስሙ ቆሬ ሁለት ቁጥር ማዞሪያ ሲሆን በዚህ የአማራ ተወላጆችን በተለያየ ምክንያት በማፈስ ከ1ሺ እስከ 2ሺ የሚደርሱ ወጣቶችን ያለ ማንም ጠያቂነትእና ያለ ምግብ ተዘግቶባቸው ይወላል። አንድ ስሙ እንዳይጠቀሰ የፈለገ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ እኔ የምኖርው እዛው አካባቢ ሲሆን ለምን እንደሚታፈሱ አንዳንድ የፖሊስ አባላትን የማናገር አጋጣሚውን አግኝቸ ነበር። ሆኖም ግን የተነገረኝ ነገር እውነት የሚመሰሉ ከእዉነት ግን የራቁ በመሆናቸው ሊያሳምኑኝ ስላልቻሉ ሀሳቡን ለአሻራ ሚዲያ ማካፈል ፈለግሁኝ።
አንድ የአማራ ተወላጅ የሆነ ፖሊስ እንደነገረኝ ከሆነ እኛ በከተማ አስተዳደሩ ትዕዛዝ መሰረት ማቆያ እንዲቆዩ በሚል በሁለት ምክንያቶች ወጣቶችን ተረክበናል።
1)የመጀመሪያው ብዙዎቻቸው የተያዙት አማራ ስለሆኑ እንጂ ለማስመሰል ከተማ አስተዳደሩ ለመወንጀል እንዲመቸው በሚከተሉት መስፈርቶች መታወቂያ ሳይዙ የሚንቀሳቀሱ፣ በልመና ስራ የተሰማሩ እና ማጅራት በመምታት በስርቆት ስራ ላይ ተሰማርተው የተገኙ በማለት ወደ ማጎሪያ እንዲጋዙ እየተደረገ ነው።
2) ሁለተኛው ደግሞ የጎዳና ተዳዳሪዎች እና ወላጅ የሌላቸዉ በመሆናቸው እንዲሁም በመዲናዋ አንድ አንድ አካባቢ ሁከት ለመቀስቀስ ሲንቀሳቀሱ እንደተገኙ አድርጎ ካስረዳኝ በኋላ የሚታፈሱት ብዛት ግን ቋሚ እንዳልሆነ እና ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል በማለት ገልፆልኛል።
በዋናነት ህንፃው የተገነባው በከተማ ከንቲባዋ አስተባባሪነት እና ኃላፊነት ሲሆን ዓለማውም የአካል ጉዳተኞች ማረፊያ ሁኖ እንዲያገለግል በሚል መጠለያ የሚል ስያሜም አብሮ ተሰጥቶት ነበር። ይሁን እንጂ ከዋለበት አላማ ወጥቶ የአማራዊያን ማጐሪያና ማስቃያ ሆኗል። በእነሱ እይታ ደግሞ ማቆያ በሚል አላማ እንዲተካ ተደርጎ ስንመለከት በየቦታው የተሰሩ እስር ቤቶች እና ማረሚያ ቤቶች በእስረኞች ስለሞላባቸው እንደ ስውር እስር ቤት እየተጠቀሙበት መሆኑን ደርሰንበታል።
አማራዊያንስ እስከመቸ በእንደዚህ አይነት ግፍ ውስጥ ይቀጥላሉ??? የታፈሱት በአማራነት ማንነታቸው እንጂ እነሱ በሚዲስኩሩት ድስኩር እንዳልሆነ ሁለችንም የምናቀው ጉዳይ ነው። እገታው እና አፈሳው በዚህ ከቀጠለ አዲስ አበባ የምትኖሩ አማራዊያን ምን ሊጠብቃችሁ እንደሚችል ለእናንተ የሚነገር ጉዳይ አይደለም ከወዲሁ ለማይቀረው የነፃነት ትግል እንድትዘጋጁ ለማሳሰብ እወዳለሁ ይላል በላከው መልዕክት።
ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም
ምንጭ ፦ አሻራ ሚዲያ
@abisiniya_times
@abisiniya_times
7.7K views14:17