የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
7.76K
የሰርጥ መግለጫ
Abbay TV 'News & Entertainment"
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
1
3 stars
1
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2023-01-18 19:05:52
1.2K views16:05
2023-01-18 18:50:05
1.2K views15:50
2023-01-18 17:20:35
@Abbay_Tv
1.2K views14:20
2023-01-18 10:58:08
ነፃ / NETSA
Till January 28, 2023
Studio 11
By Mulu Legesse.
@Abbay_Tv
1.3K views07:58
2023-01-17 20:20:51
1.4K views17:20
2023-01-17 15:26:40
ቤት የፈረሰባቸውን ሰዎች ለማነጋገር የሄዱ የዓባይ ቴሌቪዥን የቀረጻ ባለሙያዎች ታሰሩ::
በአዲስ አበባ ከተማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ቤት የፈረሰባቸውን አቤቱታ አቅራቢዎች ለማነጋገር የሄዱ የዓባይ ቴሌቪዥን የቀረጻ ባለሙያዎች ከእነአቤቱታ አቅራቢዎች ዛሬ ረፋዱን አምስት ሰዓት አካባቢ መታሰራቸውን የዓባይ ቴሌቪዥን ባለደረቦች አረጋግጠዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ቤት ፈረሰብን ያሉ አቤቱታ አቅራቢዎችን ሁኔታ በአካል ለመመልከትና ዘገባ ለመስራት በስፍራው የደረሱት የዓባይ ቴሌቪዥን ካሜራ ማንና ባልደረባው ቀረጻውን ተከልክለው በጸጥታ ሃይሎች መወሰዳቸውን ካሜራ ማኑ እስሩ በተፈጸመበት ወቅት ወደ ቢሮ በመደወል አሳውቋል፡፡
ነገር ግን መታሰራቸውንና ወደ ጣቢያ እየወሰዷቸው እንደሆነ ካሳወቀ በኋላ የጸጥታ ሃይሎች ስልኩን ስለተቀበሉት ወዲያውኑ እንደተዘጋና እንደማይሰራ የጣቢያው ባልደረቦች አስረድተዋል፡፡
ከዚያ በኋላ በተደረገ ማጣራት የታሰሩት የሚዲያው ባልደረቦች የካ አባዶ አካበቢ ወረዳ አስራ ሶስት ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገኙ ማወቅ እንደቻሉ የሚዲያው ሃላፊዎች ተናግረዋል፡፡
@Abbay_Tv
1.5K views12:26
2023-01-17 13:17:54
1.3K views10:17
2023-01-17 12:46:20
ዓውደ ርዕይ - Exhibition
January 11 - 21, 2023
Alliance Éthio-Française
የሩብ ክፍለ ዘመን ጉዞ በካፒታል እይታ
ከጥር 3 -13፣ 2015
@Abbay_Tv
1.3K views09:46
2023-01-17 12:20:47
1.2K views09:20
2023-01-17 11:23:40
አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴን በመተካት በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ተሾሙ::
አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው መሾማየውን የዲኘሎማሲ ምንጮችን ጠቅሶ አል ዐይን አማርኛ ዘግቧል።
በቅርቡ ዲፕሎማቶችን ወደ አዲስ አበባ በመጥራት ለአዲስና ነባር ተልዕኮዎች ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በቅርቡ በተለያዩ ሀገራት ተመድበው ሲሰሩ ለነበሩ አምባሳደሮች ምስጋና ከተደረገላቸው መካከል በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳዳር ታዬ አጽቀስላሴ፣ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራና ሌሎችም ይገኙበታል።
ከቀናት በፊት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴዔታ ሀላፊነታቸው የተነሱትና በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ፣ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴን ተክተው በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልክተኛ መሾማቸው ተገልጿል፡፡
አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ ከዚ በፊት በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው አገልግለዋል፡፡
ከሰሞኑ ከግብርና ሚኒስትርነታቸው የተነሱት ኡመር ሁሴን ደግሞ በተባበሩት አረብ ኢምሬት የኢትዮጵያ አምባሳደር ተደርገው ተሾመዋል፡፡
ላለፉት አመታት በተመድ የኢትዮጵያ ምክትል ቋሚ መልዕክተኛ የነበሩት አምባሳደር ማህሌት ሀይሉ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል።
አዲስ የተሸሙት አምባሳደሮችም በዛሬው ዕለት በፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ቃለ መሃላ ፈጽመው ወደ ስምሪት እንደሚገቡ ይጠበቃል፡፡
ይህ በእዲህ እንዳለ ዛሬ ከሰዓት ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊና ምክትላቸው አቶ ሰለሞን አረዳ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኃላፊነታቸው ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
@Abbay_Tv
1.1K views08:23