Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ቅዱሳን ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zkretewahdo — ዝክረ ቅዱሳን ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zkretewahdo — ዝክረ ቅዱሳን ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የሰርጥ አድራሻ: @zkretewahdo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.44K
የሰርጥ መግለጫ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
. #ዝክረ_ቅዱሳን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ
፩.ግጻዌ
፪.የዘወትር፡ስንክሳር 📖
፫.መዝሙር
፬.ዜና ቤተክርስቲያን ፡ ምክር፡ለወዳጅ እና
የተለያዩ ፡መርሃ-ግብሮች፡ይቀርቡበታል
ማንኛውንም ሀሣብ፡ አስተያየት እንዲሁም ጥቆማ በ @zikrekdusannbot ላይ
ቢያስቀምጡልን ይደርሰና

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 18:47:32
ዘጸውአ ስመከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ስምህን የጠራ መታሰቢያህንም ያደረገ እሱ በዚያ በቁርጥ የፍርድ ቀን ከንቱ ሁኖ አይቀርም።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቅድመ ዓለም የነበርክ ዛሬም ያለህ ለዘለዓለሙም ጸንተህ የምትኖር አምላክ ስትሆን የታሠሩ አገልጋዮችህን አንተ ታስረህ ፈታሃቸው በሞትህም ሞተህም የሞቱትን ወገኖችህን አስነሳሃቸው።

ለኀጡአ ምግባር

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ሃይማኖት ስንዃ ቢኖረኝ በጎ ምግባር የሌለኝ አነስተኛው አገልጋይ ማደሪያ ቤት መኖሪያ ቦታየ ከቅዱሳኖችህ ጋር ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን አቤቱ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ከከንቱ ሞት አድነኝ።ሁሉ ከንቱ ነው። የዚህ ዓለም ንብረት የከንቱ ከንቱ ነው። ሁሉም ኃላፊ ጠፊ ነውና።

ስብሐት ለከ

አቤቱ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት የምትመሰገን ለአንተ ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ምስጋና ይገባል። አቤቱ ለተራቆቱት ልብስ የምትሆናቸው ለአንተ ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል።

አቤቱ ነፍስና ስጋን አዋህደህ በምግባር ሃይማኖት አጽንተህ የምታከብራቸው ለአንተ ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል።

አቤቱ በመንግስትህ ሽረት በህልውናህ ሞት ኀልፈት የሌለብህ ለአንተ ለንጉሥ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል አቤቱ የቅዱስ አብ አካላዊ ቃል ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ኢየሱስ ሆይ ለአንተ ክብር ምስጋና ይገባል ለዘላለሙ አሜን።
240 viewsአሜን, 15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:45:57
ኦ ክርስቶስ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ኃያላን ሊቃነ መላእክት በፊትህ መቆም የማይቻላቸው። አንተን ልባቸው እንደ ድንጋይ የጠጠረ ጭፍሮች በሕዝብ አደባባይ ፊት አቆሙህ አቤቱ ! !

ፈጣሪየ ክርስቶስ ሆይ፤
ያለመጉደል እግዚአብሔር ዘሲና እግዚአብሔር ዘግብፅ እየተባልክ የምትመሰገን ዘንድ እግዚአብሔር ነህ። ዬ ዬ ዬ ስለኛ እንጨት ላይ ሰቀሉህ። አቤቱ ! አዲስ በታነፀ መቃብር መቃብር ጨምረው ቀበሩት። አቤቱ ! ! ።

ተማኀፀንኩ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
መጻጻውን መሪር ሐሞት በአጠጡህ ጊዜ ሁሉ ተፈጸመ በማለት በ 9 ሰዓት በገዛ ሥልጣንህ ነፍስህን ከስጋህ ለለየህባት ፀዓተ ነፍስህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የኃያላን ጌታ የፍጥረታትም ሁሉ ፈጣሪ እንደ መሆንህ በዚያች ነፍስህ ከሥጋህ በተለየችበት ሰዓት የሲኦል ጠባቂዋ እስኪፈራ ሞት እስኪደነግጥ ድረስ መሬት ተነዋወጠች መቃብራት ተከፋፈቱ።

ተዘከረነ እግዚኦ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አስቀድሞ ፊያታዊ ዘየማንን እንዳሰብከው አቤቱ አዳኝ ቤዛ በሚሆን መስቀልህ አስበን።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ቸር ጠባቂ ነህና እንደዓይን ብሌን ጠብቀኝ። አቤቱ እኔን መከረኛውን ኀዘንተኛውን ሰው በምስጋናህ የወይን ጠጅ አስደስተኝ አረጋጋኝ።

ኦ ዘአዖሩከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
እጅ እግርህን በመቸንከር የኛን መከራ አሸክመው በቀራንዮ በተራራ ላይ ለአቆሙህ ማቆም ሰላም እላለሁ።ነገር ሊናገር ክሂሎት ይኖረዋል።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ የመልከ ጼዴቅ ምሳሌው ካህን ሆይ አንተ ግን በአንደበቱ መናገር ሲጀምር ባርከው አክብረው በሱም ላይ ቅዱስ መንፈስህን አሳድር።
149 viewsአሜን, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:44:27
አልቦ እምሰብእ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከሰው ወገን ማንም እንደ እኔ ኃጢአት የሰራ በደለኛ የለም። እንደ አንተም ያለ መሐሪ ይቅር ባይ አምላክ አይኖርም።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ዓለማትን ሁሉ የፈጠርህ ፈጣሪ እንደመሆንህ መጠን በኃለኛው ዘመን በዓለም ላይ ለመፍረድ በምትመጣበት ጊዜ ከጎንህ በፈሰሰው ደም ኃጢአቴን እጠብልኝ አሜን።

አቄርበ ወትረ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ስለኃጢአቴ ሥርየት በጭንቅና በመከራምስጋናን ዘወትር አቀርባለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የሰማይና የምድር ጌታ እንደመሆንህ እኔ ጎስቋላው አገልጋይህን ኃጢአቴን ይቅር ብለህ ማደሪያዬን ስጠኝ እያልኩ በምለምንህ ጊዜ በዱርም ቢሆን በተራራ ላይ በአስፈላጊው ቦታ ሁሉ በፍላጎት መጠን ምግቤን አዘጋጅልኝ።

አጽምዓኒ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
መሪር የሆነ የሰቆቃው ነገር የምጽፍልህ ነኝና በጆሮህ አድምጠኝ ቅዱሳን በሆኑ እጆችህ ጹሑፌን ተቀበለኝ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
መላእክት ሊቃነ መላእክት በመንቀጥቀጥ በፊትህ የሚቆሙ አንተ በጲላጦስ አደባባይ ቆምክ አቤቱ። ዬ ዬ ዬ ስለኛ እንደዚህ ዓለም ሰው ተቆጠርክ አቤቱ። ዬ ዬ ዬ አንተ አምላክ ስትሆን ስለኛ ጎንህን በጦር ተወጋህ አቤቱ! ።

ኦ ሊቀ ካህናት

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አቤቱ የካህናት አለቃ ስትሆን እንደ ቀማኛ እንደዐመፀኛ እንደወንጀለኛ የራሄልና የልያ ልጆች የኃሊት አሰሩት።አቤቱ!።
ፈጣሪየ ክርስቶስ ሆይ፤
ስለኛ ለሞት ተላልፈህ ተሰጠህ አቤቱ።
ዬ ዬ ዬ ስለኛ በጦር ወጉህ። አቤቱ ዬ ዬ ንጹህ ክቡር ስጋህን መሬት ሸፈነው አቤቱ! ! ።
128 viewsአሜን, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:40:49 መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከሁለቱ እግሮችህ ጋር ወደ ብሔረ ሞት በፈለሱ ጊዜ በደም ቅንዋት ለተጥለቀለቁ ጉልበቶችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቃልህ የማይታበይ ዕውነተኛ አምላክ ነህ፤ አቤቱ ጌታዬ እኔን አገልጋይህን ለመጎብኘት በየጊዜው በመመላለስ ወደ እኔ ና ና አቤቱ ጌታዬ አንተ የዓለም ግርማ ሞገሱ ነህና።

ለሰኰናከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ፈጻሜ ፍቅር ወሰላም ለሆነው ተረከዝህ ሰላም እላለሁ። ዓለሙን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት የወረድህ አንተ ቸር አምላክ ነህ፡

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የአርያም ጽንዕ ኃይል ስትሆን እንደደካማ ሰው ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትሕትናህ አንክሮ ይገባል።

ለመከየድከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ያለበደልና ያለአበሳ ሰውና መላእክትን የፈጠርክ ሆይ በብረት ችንካር ለተቸነከሩት ጫማዎችህ ሰላም እላለሁ

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ጌታ መሐሪ ይቅር ባይና ቸር እግዚአብሔር እንደመሆንህ መጠን በዚያ የቁርጥ የፍርድ ቀን በምትመጣበት ጊዜ ማረኝ ይቅርም በለኝ አቤቱ በፊትህ እንደ እኔ ያለ በደለኛ የለምና

ለአጸብዓከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በለቢሰ ስጋ ለደከሙና ለወዙ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ። በጎዳና ላይ በድንጋይ ዕንቅፋት ላልተሰናከሉ ለእግሮችህ አጽፋርም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ፍለጋህ ተመራምሮ ሊገኝ የማይቻል ነው። አቤቱ የወዳጅህ የዳዊት መጽሐፍ እንደተናገረው በዚህ ዓለም ስለዕውነት ስለጽድቅህ የደከመ በወዲያኛው ዓለም የዘላለም ሕይወት እንዳለው አምናለሁ ተስፋም አደርጋለሁ።

ለቆምከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አይሁዶች ተሰባስበው በቀራንዮ አደባባይ ለአቆሙት አካለ ቆምህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ግዙፍ ሥጋን በተላበሰ አንደበቴ ልመናዬን ሳቀርብልህ አሳልፈህ ለጠላት አትስጠኝ።እንዳንተ ያለ ጠቃሚ ዘመድ በቂ ወገን አይገኝምና።

ለመልክእከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ለጻድቃን ያይደለ ኀጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ሥነ መልክእህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በየጊዜው በነጋ በጠባ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ። በመስቀል ላይ ሳለህ አባት ሆይ፤ ይቅር በላቸው በማለት የተናገርከውን የቸርነትና የርኀራኄ ቃል አስቀድሜ ሰምቻለሁና።

ለፀአተ ነፍስከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በመስቀል ላይ ልዩ ልዩ አምላካዊ ተአምራትንና ሕማማተ መስቀል ከተፈጸመ ቡኃላ በገዛ ሥልጣንህ ለተፈጸመው ጸዓተ ነፍስህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ዓለምን ለማዳን በተሰቀልክበት በዚያን ሰዓት እንሆ ጌታዬ ሆይ፤ ፀሐይ ብርሃኑን ከመስጠት ተከልክሎ ጊዜው ጨለመ ጨረቃም ደም ሆነ።

ለግንዘተ ሥጋከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከጽጌረዳ መዓዛ ይልቅ መዓዛ ላለው ግንዘተ ሥጋህ ሰላም እላለሁ። በኢየሩሳሌም አደባባይ ለሚገኘው መካነ መቃብርህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ሰይጣናዊ በሆነ በይሁዳ ወገኖች ቅናት ሞተህ የሔዋን ልጆች ባልተቀበሩበት አዲስ የሚሆን በታነፀ የሕንጻ መቃብር ተቀበርህ። አቤቱ ሞት የማይገባህ ላንተ ምስጋና ይገባል።

ለትንሣኤከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የመቃብር ጠባቂ ጭፍሮችን አሸብሮ የጻድቃንን ትንሣኤ ለገለጠው ትንሣኤህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በልዩ ትንሣኤህ ጨለማን ካስወገድህ ቡኃላ በግብር አምላካዊ በዝግ ቤት ገብተህ ደቀመዛሙርትህን በጦር የተወጋውን ጎኔን በችንካር የተቸነከሩ እጅ እግሬን ተመልከቱ አልካቸው።

ለትንሣኤከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከእንቅልፍ እንደመንቃት ለሆነ ትንሣኤህ ሰላም እያልኩ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ተአምራትህን እናገራለሁኝ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ለአዳም ልጆች መድኀን እንደመሆንህ መጠን የእኔን የደካማውን አገልጋይህን ልመና ተቀብለህ አቤቱ ከዚያ ርጉም ከሚሆን ጠላቴ እጅ አድነኝ።

ለዕርገትከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በዓውሎ ንፋስ በእሳተ ነበልባል አምሳል መንፈስ ቅዱስን ትልክልን ዘንድ በነጎድጓድና በመባርቅት የሠረገላ ዘባን ለተከናወነ ዕርገትህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በአንዲት መንግሥትህ መንግሥቱን ለዘላለም አገዛዙም ለትውልደ ትውልድ ነው እያሉ ሰማያውያን መላእክት በየዕለቱ በየሰዓቱ ያመሰግኑሃል።

ለዕርገትከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የቃል ኪዳኑን ሥነ ሥረዓት ለፈጸመ ዕርገትህና ሁሉን ለማዘጋጀት በኃለኛው ዘመን አመጣጥህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቅድመ ዓለም በጌትነቱ ክብር ከአባትህ ዘንድ የነበረ ወደዚህ ዓለም በዓውሎ ነፋስ አምሳል የላክኸው እሱ መንፈስ ቅዱስ የኃጢአቴን እሾህ በማቃጠል አቤቱ እሱ ኃይሉን ይግለጽ።
113 viewsአሜን, 15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:40:49 ለመላትሒከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ሕማመ ተጾፍዖን ለመቀበል ለተዘጋጁ ጉንጮችህ ሰላም እላለሁ። ኀሊናን ደስ ለሚያሰኙ አዕናፍህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ሠራዊተ መላእክት እየተንቀጠቀጡ በፊትህ የሚቆሙ አንተ በቀያፋና ሐና አደባባይ ቆምህ። አቤቱ የኔ ጥፋት በአንተ ዘንድ ተፈላጊ አይደለምና እንደሰማሁትና እንደማውቀውም ሁሉ በመስቀልህ ቤዛነት አድነኝ።

ለአፉከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አቤቱ እንደከረመ የወይን ጠጅ የሐሞትን መራራነት ላጣጣመ አፍህ ና ከናፍርህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ አምላካዊ ተአምራት የማድረግ ስልጣን በአንተ እጅ በመሆኑ። ዳግም በምትመጣባት በዚያች ዕለት ሑሩ እምኔየ የምትለውን የፍርድ ውሳኔ እንዳታሰማኝ በቸርነትህ እማፀናለሁ።

ለአስናኒከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በቀራንዮ አደባባይ በመስቀል ላይ ሣለህ ስለዓለም ነፃ መውጣት የሰበከ አንደበትህና መለኮታዊ አስናኖችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቃልህ የማይታበል የማይለወጥ ነውና መልአከ ሞት ነፍሴን በፊትህ ባቆማት ጊዜ አቤቱ ገጸ ምሕረትህን አትመልስብኝ።

ለቃልከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አባት ሆይ፤ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ። በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህንም በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እሳት ትንፋሽህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ከዚያ እስከዚህ ድረስ የሰራሁትን ኃጢአቴን ይቅር በል። አቤቱ ቅዱስ ስጋህን ከበላሁ ክቡር ደምህን ከጠጣሁ ቡኃላ ነፍሴ ጥፋት እንዳያገኛት በፍጹም ትጋት ደጅ እጠናለሁ።

ለጕርዔከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ክቡር ልዑል ለሚሆን ጕርዔህ ሰላም እላለሁ። በገመድ እየሣቡ ለጎተቱት ክሣድህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው ለሰው ልጅ ደህንነት እንደመሆኑ መጠን ስለእናትህ ስለድንግል ማርያም ብለህ ምሬሃለሁ ይቅር ብየሃለሁ በለኝ። ከአንተ በቀር ቸር ይቅር ባይ የለምና።

ለመታክፍቲከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በጎልጎታና በቀራንዮ አደባባይ አርዑተ መስቀልን ተሸክመው ለተንገላቱ መተክፍትህ ሰላም እላለሁ። ዙፋኑን በዘባነ ኪሩቤል ለአዘጋጀ ዘባንህም ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በቀል የሌለብህ አምላክ እንደመሆንህ በቅዱሳኖች በወዳጆችህ አማላጅነት እማፀናለሁ። ስማችሁን የጠራ እምርላችኃለሁ ስትል ቃል ኪዳን ገብተህላቸዋልና።

ለእንግድዓከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የአዳምን ዘር ለማዳንና በጠቅላላው ለዓለም ቤዛ ለመሆን ሐፃውንተ መስቀልን ለታቀፉ ክንድህና ደረትህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ለሰውነቴ መልካሙን የዕረፍት ጊዜ ስጣት። አቤቱ ሰውነቴን፤ ነፍሴን የሚፃረሯትን ጠላቶቼን ሁሉ፤ የሚያደርጉትን አያውቁምና አባቴ ሆይ ይቅር በላቸው ብለህ እንዳስተማርከን ይቅርታ ታደርግላቸው ዘንድ እማጸናለሁ።

ለአእዳዊከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ለቤዛ ዓለም ስትል ለፈሰሰው ደምህ፤ ለተቸነከሩና በደም ለተጠመቁ እጆችህ ሰላም እላለሁ። በሌሊት የሚዘዋወረውን ድንገተኛ ጠላትና በቀን የሚጻረረውን የቀትር ኃያለ አጋንንት ለሚያዳሽቀው መለኮታዊ ግርማህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በጎ ነገርን አሰጀምረህ የምታስፈጽም ቸር አምላክ ነህ። አቤቱ ከጎንህ የፈሰሰው ደመ መብረቅ ከላይ ወደታች በተቈለቈለ ጊዜ ድምፀ ጉህናው ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ አስተጋባ።

ለኵርናዕከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በቅዱስ መስቀል ላይ በተሰቀልክ ጊዜ በግራና በቀኝ ተዘርግተው ለተንሰራፉ ክንድህና ውርቾችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ደዌ መከራ ከሌለበት፤ ተድላ ደስታ ከአለበት ኤዶም ገነት ታገባኝ ዘንድ እለምንሃለሁ።

ለእራኀከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የእናታችን የሔዋንን በደሏን ይቅር ትልላት ዘንድ መከራን ለተቀበሉ መዳፎችህና ዓለማትን ሁሉ በመለኮታዊ ጥበብ ለፈጠሩ ዓሥሩ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪየ ክርስቶስ ሆይ፤
የኃጥአን ነፍስ መጠጊያ አንተ ነህ፤ለዓለምም የምታበራላቸው እውነተኛ ፀሐይ አንተ ነህ።

ለአጽፋረ እዴከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የዓሠርቱ ቃላተ ኦሪት ትእዛዛት ለተጻፉባቸው ንዑዳት ክቡራት ለሚሆኑ ለእጆችህ አጽፋር ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ክቡር ዳዊት እንደተናገረው ጠላቶቼ ሰውነቱ ዱር ለዱር ተቅበዘበዘ እያሉ እንዳይዘባበቱብኝ በየጊዜው በየሰዓቱ በየዕለቱ ልመናዬን ሳቀርብልህ ፈጥነህ ተቀበለኝ እንጂ ቸል አትበለኝ።

ለገቦከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ኀዘን ትካዜን ለሚያስወግድ መለኮታዊ ጎንህ ሰላም እላለሁ። በዓለሙ ሁሉ በጭንቅና በመከራ ላይ የሚገኙትንም ለሚያረጋጋ አምላካዊ ከርስህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
መድረቅ መጽነፍ የሌለበት ባሕረ ምሕረት እንደምሆንህ የቸርነትን ቃል መቼ ታሰማኝ ይሆን? እያልኩ ሁል ጊዜ አምላኬ አምላኬ እላለሁ።

ለልብከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ናዝራዊ የተባልክ ለአንተ ለእግዚአብሔር ነቢይ ወመንፈሳዊ ለተባልክ ለአንተ ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ልቡና ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ስለትሕትና ሕጻን ወአረጋዊ እየተባልክ የምትመሰገን አንተን በመስፍኑ በጲላጦስ አደባባይ እንደወንጀለኛ አገልጋይ ባሪያ የሌዊና የይሁዳ ልጆች የሚሆኑ ካህናት እንዴት ሊገርፉህ ተበረታቱ አቤቱ ለትዕግሥትህ አንክሮ ይገባል።

ለኵልያቲከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
እንደ አጥቢያ ኮከብ በግራ በቀኝ ሆነው ለሚያበሩ ሁለት ኵልያቶችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ እግዚአብሔር እየተባልክ ትመካለህ። አቤቱ አንተ ክርስቶስ ለኃጥአን ስንዃ ሕይወታቸው ነህና፤ አቤቱ ስንልህ በከንቱ እንዳንጠፋ ጠብቀን።

ለኀሊናከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ዳግመኛ ከሰሜን እስከ ደቡብ በዓራቱም ማዕዝነ ዓለም የብርሃኑ ጸዳል ለሚንጸባርቀው ኀሊናህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በዘባነ ኪሩቤል ላይ ዙፋንህን ዘርግተህ የተቀመጥህ አንተ ነህ። የአብን ፈቃድ ትፈጽም ዘንድ ከሰማየ ሰማያት ወደዚህ ዓለም የመጣህ አንተ ነህና ክቡር ምስጉን አምላክ ነህ።

ለአማዑቲከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የኃጥኡን ሰው ውሳጣዊና አፍአዊ ሰውነቱን ለሚቀድሰው ንዑድ ክቡር ለሚሆን ውስጣዊ ገንዘብህና ለአማዑትህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ከዚህ ዓለም ጥፋትና ጥል ፡ ጭቅጭቅና ንዝንዝ ሁሉ አድነኝ። በሰማይና በምድር፤ በባሕርና በየብስም ቢሆንም ያለአንተ ቸር ሰው ወዳጅ ንጉሥ የለምና።

ለሕንብርትከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በአምሳለ ቅዱስ መስቀል ማዕተብነ፤ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ለተማተበው ሕንብርትህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ከችግርና ከፈተና አድነኝ፤ አባትህም በምስሐ ደብረጽዮን በሚያደርገው ታላቅ የምሳ ግብዣ ላይ ይዘኸኝ ግባ ከአንተ በቀር ሌላ የማውቀው ዘመድ የለኝምና።

ለሐቌከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የሲኦልን በር የናሱን መዝጊያ ቀጥቅጠህና ሰባብረህ የብረቱንም ቁልፍ እንደ ሰም አቅልጠህ ነፍሳትን ከሲኦል በአወጣህበት ሰዓት መለኮታዊ ዝናርን ለታጠቀ ወገብህንና ኃይለአርያምን ለተጎናጸፉ አቍያጾችህም ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
መሐሪ ይቅር ባይ አንተ እግዚአብሔር እንደመሆንህ መጠን በምሄድበት መንገድ ሁሉ ቀናውን ጎዳና ምራኝ። የጽድቁንና ዕውነተኛውን መንገድ ፈጽሞ ለማወቅ አልችልምና።

ለአብራኪከ
111 viewsአሜን, edited  15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:40:20
መልክአ መድኃኒዓለም

ለዝክረ ስምከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ምስጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማዕታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበትን መራራ ሀሞትን ስለ እኔ ሕይወት የጠጣህ የአቀረብኳትን አነስተኛ የምስጋና መባየን በቸርነትህ ተቀበል።

ለስእርተ ርእስከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
እኛን ስለማዳን መከራን ለመቀበል ዘንበል ላለው ርእስህና ስእርተ ርእስህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ከሰማየ ሰማያት ወርደህ ከድንግል ማርያም ተወልደህ በሥጋ ብእሲ በሕጻን አርአያ በተገለጽክበት ወራት እናታችን ሔዋንን ያሳተ ከይሲ ዲያቢሎስ ፈራ ደነገጠ በኀዘንና በልቅሶም ተዋጠ።

ለገጽከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከሁለቱ ቀራንብቶችህ ጋር ለሚያንባርቀው አመጸኛንና ከዳተኛን በማስደንገጥ ብቻ ለሚያንበረክከው ለገጽህ ግርማ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የኃጢአትን ማእበል ባሕር እንደምትገስፀው መጠን። አቤቱ በገሃነመ እሳት ከመቃጠልና ከሲኦል ትላትል ቁንጥጫ በቸርነትህ አድነኝ።እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ እንደጋለ ብረትና እንደተሣለ ምሳር ነውና።

ለአዕይንቲከ

መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የቅዱሳንን ጥሪ ለሚሰማ ዕዝንህና ድሆችን ለሚመለከቱ ዓይኖችህ ሰላም እላለሁ።

ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በላይ በዘባነ ኪሩቤል ተቀምጠህ የባሕሮችን ጥልቀት ትመለከታለህ። አቤቱ ሰውነቴን ከሰይጣን ፈተና ከአመፀኛ ከተንኮለኛ አድናት። አቤቱ ባሕሩን አድርቀህ ደረቁን ሳር የምታለመልም ክሂሎት ያለህ አሸናፊ አምላክ ነህና።
106 viewsአሜን, 15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:31:45
ነገደ ሥልጣናት (ሱርያል)፦ ያላቸው ከኤረር መኻከል በኹለተኛዋ በራማ ውስጥ ከሚኖሩት፡፡ ከ፴ው ነገድ ውስጥ ሲኾኑ፤ ስለነዚኽ ነገደ መላዕክት ሊቁ ኤጲፋንዮስ በአክሲማሮስ ላይ ሲገልጽ "ወለሣልስ ጾታ ዐሠርቱ ስሞሙ ሥልጣናት ወሊቆሙ ሱርያል መልአክ ወአንበሮሙ በሣልስ ሰማይ እሉ እሙንቱ እለ ይጸውሩ አብዋቀ ብርሃን ወያደምፁ ለመላእክት በጊዜ ቅዳሴሁ ወስባሔሁ ለእግዚአብሔር ለዘክሮቱ ይደሉ ሰጊድ" ይላል ለስም አጠራሩ ስግደት ይግባውና ልዑል እግዚአብሔር ሦስተኛ ዐሥሩን ነገድ ሥልጣናት ሲላቸው አለቃቸው መልአኩ ሱርያል ይባላል፤ እነዚኽም የብርሃን ነጋሪት የሚይዙ ሲኾኑ መላእክትን በስባሔ ሲያነቁ ሲያተጉ የሚኖሩ እነዚኽ መላእክት ሲኾኑ፤ በራማ በሦስተኘው ከተማ አስፍሯቸዋል። ምንጭ፦ ዶክተር ሮዳስ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ተአምኆ ቅዱሳን በተረጎመበት ላይ።
126 viewsአሜን, 15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:29:54
‹‹ወሳሙኤልኒ ምስለ እለ ይጼውዑ ስሞ ይጼውዕዎ ለእግዚአብሔር ውእቱኒ ይሰጠዎሙ ወይትናገሮሙ በዐምደ ደመና።››

‹‹ሙሴና አሮን በካህናቱ ዘንድ፥ ሳሙኤልም ስሙን በሚጠሩት ዘንድ ናቸው፤ እግዚአብሔርን ጠሩት፥ እርሱም መለሰላቸው።በደመና ዓምድም ተናገራቸው፤ ምስክሩንና የሰጣቸውን ትእዛዝ ጠበቁ።››
መዝሙር ፺፰፡፮
116 viewsአሜን, 15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:25:25 ✞ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ✞

""" ነሐሴ 27ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት """

+" 12ቱ አበው ደቂቀ እሥራኤል "+

=>እነዚህ አበው የአብርሃምና የይስሐቅ የልጅ ልጆች የያዕቆብ ደግሞ ልጆች ናቸው:: ትውልድ ከአዳም እስከ ቅዱስ ያዕቆብ አንድ ሐረግ ይዞ መጥቶ እዚህ ላይ ሲደርስ ይበተናል:: አባታችን ያዕቆብን እግዚአብሔር ሲባርከው እሥራኤል አለው:: ትርጉሙም "ሕዝበ እግዚአብሔር: ወልድ ዘበኩር (የበኩር ልጅ): ከሃሊ: ነጻሪ (አስተዋይ) እንደ ማለት ነው::

+ይህ ቅዱስ አባት ለድንግል ማርያም ቅድመ አያት ከመሆኑ ባሻገር ነቢያትን: ካህናትን: ነገሥታትንና መሣፍንትን ወልዷል:: ከወንድሙ ኤሳው ጋር ተጣልቶ ወደ ሶርያ በሔደ ጊዜ ከ2ቱ ሚስቶቹ (ልያና ራሔል) 8 ልጆችን: ከ2ቱ የሚስቶቹ ደንገ ጥሮች (ዘለፋና ባላ) 4 ልጆችን: በድምሩ 12 ልጆችን ወልዷል::

#‎ልያ የወለደቻቸው:-
1.ሮቤል
2.ስምዖን
3.ሌዊ
4.ይሁዳ
5.ይሳኮር እና
6.ዛብሎን ይባላሉ::

#‎ራሔል የወለደቻቸው:-
7.ዮሴፍና
8.ብንያም ይባላሉ::

#‎ባላ :- 9.ዳን እና
10.ንፍታሌምን ስትወልድ

#‎ዘለፋ :- ደግሞ 11.ጋድና 12.አሴርን ወልዳለች::

#‎12ቱ ደቂቀ እሥራኤል (ያዕቆብ) ማለት እኒህ ናቸው::

+ከ12ቱ በቅድስና ዮሴፍ ከፍ ቢልም እግዚአብሔር ለክህነት ሌዊን: ለመንግስት ደግሞ ይሁዳን መርጧል:: ከእነሱ ዘርም ዓለምን ለማዳን ተወልዷል:: 10ሩ አበው በተለይ በዮሴፍ ላይ ግፍ ሠርተው የነበረ ቢሆንም በኋላተጸጽተዋል:: እነሆ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ታስባቸዋለች:: (ዘፍ. ከ28-31)

+" ነቢዩ ቅዱስ ሳሙኤል "+

+እሥራኤል ከግብፅ ባርነት ወጥተው ከነዓንን ከወረሱበት ዘመን ጀምረው መሳፍንትና ካህናት ያስተዳድሯቸው ነበር:: በወቅቱ ታዲያ ክህነት ከምስፍና ተስማምቶለት ኤሊ የተባለ ሊቀ ካህናትና ልጆቹ (አፍኒና ፊንሐስ) ያስተዳድሩ ጀመር::

+በዘመኑ ደግሞ ማሕጸኗ ተዘግቶባት ዘወትር የምታለቅስ ሐና የሚሏት ደግ ሴት ነበረች:: እግዚአብሔር የእርሷን ጸሎትና የሊቀ ካህናቱን ምርቃት ሰምቷልና ቅዱስ ልጅን ሰጣት:: "ሳሙኤል" አለችው:: "ልመናየን አምላክ ሰማኝ" ማለት ነውና::

+ሐና ስዕለቷን ትፈጽም ዘንድ ሳሙኤልን በ3 ዓመቱ ለቤተ እግዚአብሔር ሰጠችው:: በዚያም ስብሐተ እግዚአብሔርን እየሰማ: ማዕጠንቱን እያሸተተ: ከደብተራ ኦሪቱ ሳይለይ በሞገስ አደገ:: የኤሊ ልጆች (አፍኒና ፊንሐስ) በበደል ላይ በደልን አበዙ::

+ወቅቱ የአሁኑን ዘመን ይመስል ነበር:: ሁሉም ሰው ክፋተኛ የሆነበት በመሆኑ እግዚአብሔር ርቆ ስለ ነበር ትንቢትና ራዕይ ብርቅ ነበር:: አምላክ ተቆጥቷልና ሳሙኤልን በሌሊት 3 ጊዜ ጠራው:: ነቢዩም ታጥቆ የፈጣሪውን ቃል ሰማ:: በዚሕም የተነሳ ታቦተ ጽዮን ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ ተማረከች:: ከ34ሺ በላይ ሕዝብ በኢሎፍላውያን አለቀ:: አፍኒና ፊንሐስም ተገደሉ:: ኤሊም ወድቆ ሞተ::

+ከዚህች ቀን በኋላ ቅዱስ ሳሙኤል በእሥራኤል ላይ ነቢይና መስፍን ሆኖ ተሾመ:: በዘመኑ ሁሉ እንደሚገባው እየኖረ: የእግዚአብሔርን ለእሥራኤል: የእሥራኤልን ለእግዚአብሔር ሲያደርስ ኑሯል:: ሕዝቡ ንጉሥ በፈለጉ ጊዜ ሳዖልን ቀብቶ አነገሠላቸው:: እርሱ (ሳዖል) እንደ ሕጉ አልሔደምና ፈጣሪ ናቀው::

+ሳሙኤል ግን ደግ አባት ነውና ክፋተኛውን (ሳዖልን) ከጌታው ጋር ያስታርቅ ዘንድ ብዙ ደከመ: አለቀሰም:: እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን:- "አትዘን! እንደ ልቤ የሆነ: ፈቃዴን የሚፈጽም ዳዊትን አግኝቸዋለሁና እርሱን በእሥራኤል ላይ አንግሠው" አለው::
ቅዱስ ሳሙኤልም ወደ ቤተ ልሔም ሔዶ: ከእሴይ ልጆችም መርጦ ልበ አምላክ ዳዊትን ቀባው: አነገሠውም::

+ቅዱስ ሳሙኤል በተረፈው ዘመኑ ለፈጣሪው እየተገዛ ኑሯል:: ነቢዩ ዘወትር ከእጁ የሽቱ ሙዳይና የቅብዐት እቃ (ቀንድ) አይለይም ነበረ:: እነዚህም የድንግል ማርያም ምሳሌዎች ናቸውና አባ ሕርያቆስ:-
"ሙዳየ ዕፍረት ወቀርነ ቅብዕ ዘሳሙኤል" ብሎ አመስግኗታል::

+ነቢዩም በወገኖቹ መካከል በዚሕች ቀን አርፏል:: እሥራኤልም አልቅሰውለታል:: ዛሬ ቅዱሱ ነቢይ ለአገልግሎት የተጠራበት ቀን ነው::

+" ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት "+

+ከታላላቅ ሊቃናት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሱርያል ክብሩ ብዙ ቢሆንም ብዙ ምዕመናን አያውቁትም:: የመላእክት መዓርግ ሲነገር ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤል ብሎ ቀጥሎ የሚመጣው ሱርያል ነው::

+በ3ቱ ሰማያት ካሉት 9ኙ ዓለመ መላእክት የአንዱ (የሥልጣናት) መሪ (አለቃ) ነው:: መልአኩ እጅግ ርሕሩሕ እና ተራዳኢ ነውና አንዘንጋው:: ለኖኅ መርከብርን ያሳራው: ከጥፋት ውሃም ያዳነው ይህ ቅዱስ መልአክ ነው::

+በገድለ ሰማዕታትም ላይ እንደተጠቀሰው የሰማዕታት ረዳትና አዳኝም ነው:: ቅዱስ ሱርያል በሌላ ስሙ "እሥራልዩ" ይባላል:: "የእሥራኤል ረዳት" እንደ ማለት::

=>ቸሩ አምላከ ቅዱሳን ስለ አባቶቻችን ብሎ ይማረን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

=>ነሐሴ 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1."12ቱ" ደቂቀ ያዕቆብ (እሥራኤል)
2.ቅዱስ ሳሙኤል ነቢይ (የተጠራበት)
3.ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላእክት
4.ቅዱስ ብንያሚንና እህቱ አውዶከስያ (ሰማዕታት)
5.ቅዱስ ፊቅጦርና እናቱ ሣራ
6.አባ ባስልዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮዽያ (የተሾሙበት)

=>+"+ እነዚህም ሁሉ አሥራ ሁለቱ የእሥራኤል ነገዶች ናቸው:: አባታቸው የነገራቸው ይህ ነው:: ባረካቸውም:: እያንዳንዳቸውን እንደ በረከታቸው ባረካቸው:: +"+ (ዘፍ. 49:28)
=>+"+ በመንፈስም ወደ ታላቅና ወደ ረዥም ተራራ ወሰደኝ:: የእግዚአብሔርም ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ: ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ . . . አሥራ ሁለት ደጆችም ነበሯት:: በደጆቹም አሥራ ሁለት መላእክት ቆሙ:: የአሥራ ሁለቱም የእሥራኤል ልጆች ነገዶች ስሞች ተጽፈውባቸው ነበር:: +"+ (ራዕይ. 21:11)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ዝክረ ቅዱሳን ማኀበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

@zkretewahdo
@zkretewahdo
@zkre_tewahdo_bot
140 viewsአሜን, 15:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:20:27 ምስባክ ዘቅዳሴ

‹‹ወሳሙኤልኒ ምስለ እለ ይጼውዑ ስሞ ይጼውዕዎ ለእግዚአብሔር ውእቱኒ ይሰጠዎሙ ወይትናገሮሙ በዐምደ ደመና።››

‹‹ሳሙኤልም ስሙን በሚጠሩት ዘንድ ናቸው፤ እግዚአብሔርን ጠሩት፥ እርሱም መለሰላቸው።በደመና ዓምድም ተናገራቸው፤››
መዝሙር ፺፰፡፮

የዕለቱ ወንጌል

ዮሐንስ ፲፪፡፳፮-፴፩
፳፮ የሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፥ እኔም ባለሁበት አገልጋዬ ደግሞ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል።
፳፯ አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ።
፳፰ አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም፦ አከበርሁት ደግሞም አከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።
፳፱ በዚያ ቆመው የነበሩትም ሕዝብ በሰሙ ጊዜ፦ ነጐድጓድ ነው አሉ፤ ሌሎች፦ መልአክ ተናገረው አሉ።
፴ ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ ይህ ድምፅ ስለ እናንተ መጥቶአል እጂ ስለ እኔ አይደለም።
፴፩ አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል፤


✥✥✥ ️ቅዳሴ፦ ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ።


@zkretewahdo
@zkretewahdo
@zkretewahdo
137 viewsአሜን, 15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ