የደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት - በተማሪዎች ውጤትም ሆነ በትምህርት ቤት ደረጃ በተመዘገበው ውጤት ከሀገር አቀፍ አንደኛ ነው!
ወንድማችን ውብሸት ሙላት ባጋራን መረጃ መሠረት ፦
በትምህርት ቤቱ አጠቃላይ የተፈተኑ ተማሪዎች ብዛት- 69 ሲሆን እስካሁን የ68ቱ ተማሪዎች ውጤታቸው ታውቋል፡፡
በዚህም መሠረት የተማሪዎቹ ዝርዝር ውጤት፦
~ 25 ተማሪዎች - ከ600 በላይ
~ 40 ተማሪዎች - ከ 500 - 599
~ 3 ተማሪዎች 450-499 ማስመዝገባቸው ታውቋል፡፡ ውጤቱ ያልታወቀው የአንድ ተማሪ ብቻ ነው።
በቅርብ ጊዜ ትልቅ ራዕይን ሰንቆ እውን በተደረገና ብዙ ርቀት ሳይጓዝ ከኮቪድ በኃላ ፥ ለረዥም ጊዜ በጦርነት ውስጥ በቆየውና ብዙ ውድመት ባስተናገደ አዳሪ ት/ቤት ፥ ይህን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ እጅግ አስገራሚ ነው፡፡ ይህን ትምህርት ቤት ማሳደግና ማጎልበት ብሎም ማስፋፋት ለወደፊቱ የሀገር ተረካቢ የሚሆኑ ብቁ ዜጎችን ለመፍጠር እንደሚያስችል የተገኘው ውጤት በቂ ማሳያ ነው!