Get Mystery Box with random crypto!

'ርዕሰ አንቀጽ' '…ከጠዋቱ የቀጠለ… '…ውይይቱ በተቋረጠ ቀን የቀረ የጎንደር ፋኖ አልነበረ | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ርዕሰ አንቀጽ"

"…ከጠዋቱ የቀጠለ…

"…ውይይቱ በተቋረጠ ቀን የቀረ የጎንደር ፋኖ አልነበረም። እኔም የሆዴን በሆዴ፣ የልቤን በልቤ ይዤ ለጀማው ሰላምታ አቀረብኩ። ሁላቸውም ሰላምታዬን ተቀበሉኝ። እንደልማዳችን ማን መጣ? ማንስ ቀረ ብዬም ጠየቅኩ። አንደኛው ወገን ብቻ መምጣቱን፣ ሌላኛው ወገን ግን ዛሬም አለመቅረቡ ተነገረን። የቀሩበትም ምክንያት ተነገረ። የቀረበውም ምክንያት አሳማኝ ስለመሰለኝ ምክንያታቸውን ተቀብለን በይደር አቆየነው።

"…መሽቶ ነጋ። በሁለተኛው ቀን የተባለው የቀጠሮ ሰዓት ደረሰ። ሁላችንም በሰዓታችን ተገኘን። እንቅልፍ እንዳይጥለው ቀዝቃዛ ውኃ እግሩን ዘፍዝፎ የሚቀመጥም ነበር። የሆነው ሆኖ ዛሬም ግን አንደኛው ወገን አልመጣም። አለመምጣቱን ሳውቅ ዛሬም ለጸሎት እንነሣ ብዬ ቀቀሪውን አዘዝኩ። ጸሎት አድርገን ከፈጸምን በኋላ ግን የመረረ ንግግር አደረግኩ። ሽምግልናው የደረሰበትን አጠቃላይ ሂደትም ለሕዝብ ይፋ አድርጌ እቋጨዋለሁ ብዬም ሽምግልናውን አክብረው ለቀሩቱ ገለጥኩ። እናንተ ግን እግዚአብሔር ያክብራችሁ በርቱ በማለትም ተሰናበትኳቸው። ለምንአልባቱ ተፀፅተው ከተመለሱ፣ ለጎንደር አንድነት፣ ለዐማራ አንድነት አስበው ከተመለሱ አለሁ በእገሌ በኩል ልትጠሩኝ ትችላላችሁ ብዬ ነበር የተሰናበትኩት።

"…መሸ፣ ነጋ በሌላኛው ቀን ዛሬ ሆነ። የሽምግልናውን ውጤት ለሕዝብ ይፋ የማደርገው ነገ ቢሆንም ዛሬ ለነገው ዐዋጄ የመግቢያ ምልክት የሚሆን መብረቃዊ ብልጭታ ያለው ምልክት የመስጫ ዕለቴ ነበር።

"…የጎንደሩን ብቻ ሳይሆን የሸዋዎቹም የእርቁ ነጠላ ተሸምኖ አልቆ ቁጭቱ፣ መቋጭያው ላይ አንደኛው ወገን አስከ ዛሬዋ ድረስ አልተሳካለትም ነበር። እርቁ አልቆ፣ ይቅር መባባሉ አልቆ መቋጫው ላይ ሰይጣን ገብቶ ግግም ብሎም ነበር። በመሃል ሰይጣን የሸዋውን የተሰበሰበ ምርጥ ስንዴ ለመበተን ያልደከመው ድካም፣ ያል ጫራው ጭረት፣ ያልቆፈረው ጉድጓድ አልነበረም። እሳቱን እንደማጥፋት ቤንዚን ይዘው ለማቀጣጠል የሚሮጠውን መንጋ እያየሁ እታዘብ ነበር። ዐውቆ በድፍረት፣ ሳያውቅ በስህተት የተፈጠረን በደል ኃጢአት ይቅር እንደማለት ድንጋይ ይዞ ወጋሪው ለጉድ ነበር። እኔ ግን በደለ፣ ኃጢአት ሠራ የተባለውን ሁላ እያቀረብኩ ሁለተኛ እንዳትበድል የሚለውን የአምላኬን ወርቃማ ቃል እየጠቀስኩ በሰላም ኑሩ እያልኩ በመሸኘት በማጽናናትም በሁለቱም በኩል የሚረጨው ቤንዚል አካባቢ እሳትና ክብሪት እንዳያልፍ እየተሟገትኩ አይደረስ የለም ዛሬን ደረስኩ።

"…ጎንደሮችም ደወሉ። በቃ ልክ አላደረግንም። የጎንደር ታጋዮችንም ደም፣ የአጼ ቴዎድሮስንም አፅም አስወቅሰናል፣ በንፁሐን ዐማሮች በሚፈሰው ደማቸውም ጭምር ተወቅሰናል እናም ከወንድሞቻችን ተመልሰን በይቅርታ ለመቋጨት ተመልሰናል። አንተንም ዘመዴንም፣ ታዛቢ ሽማግሌዎችንም ቅር አሰኝተናል፣ እናም እንመለስና እንቋጨው በማለት ለእርቅ እጃቸውን ወደላይ ከፍ አድርገው ተማርከው ተመልሰዋል። እኔም የጠፋው ልጅ በተገኘ ጊዜ አባት የተደሰተውን ደስታ በሚያስንቅ መልኩ ተደስቼ እጄን ለሽምግልናው ዘርግቼ የቀጠሮውን ቀን በመጠባበቅ ላይ እገኛለሁ።

"…ሸዋዎቹም ደወሉ። አነጋገሩኝም። በኔትወርክ፣ በእኔ ያለመመቸት፣ በስንፍና፣ በቸልተኝነት የዘገየውንና የታዘዙትን በዛሬው ዕለት ፈጸሙ። አቅርቡ የተባሉትንም በሙሉ አቀረቡ። ተነጋገርን፣ ተወያየን፣ በደስታም ተቀጣጠርን። ውጤቱን በጋራ እናየዋለን። ሁሉም ውይይቶቻችን የተቀረጹ ናቸው። ታሪካዊ ቀረጻ። ለትውልድ የሚተላለፍ ቀረጻ ነው። እናም አሁን ልቤ አርፏል።

"…የእኔ ሽምግልና በሁሉም ጥሪና ምርጫ ነው። ሲያጠፉ በእኔ መገሰጽን መርጠው፣ ፈቅደው ነው የመረጡኝ፣ የጠሩኝም። ብዙ ሰዎች እሱ ምን አገባውም ሲሉ አደምጣለሁ። በተለይ ርእዮተ እስክንድር የሚለው የኋትስ ግሩፕ ላይ እሱ ምን አገባው? አለምአቀፍ የግጭት አፈታት አልተማረ፣ ማንበብና መጻፍ አይችል፣ እንግሊዝኛ አይናገር አይሰማ አይጽፍ፣ አያነብ፣ ምን አገባውና ነው እሱ ብለው ሲንጨረጨሩብኝ እንደሚውሉም አያለሁ፣ እመለከታለሁም። እግዚአብሔር ያሳያችሁ ጋሽ መሳፍንትን፣ ጋሽ ባዬን፣ ጋሽ መከታውንና ጋሽ አሰግድን ለማስታረቅ እንግሊዝኛ ማወቅ መስፈርት ሲሆን። ኮተታም ሁላ። ለማንኛውም በአማርኛ ቋንቋ እየተወያዩ ከዚህ ደርሰዋል።

"…ቲክቶክ ላይ አብዮት የሚያቀጣጥሉ፣ የሚያጫጭሱ፣ ፌስቡክ ላይ አቧራ የሚያጨሱ የትየለሌ ናቸው። ዐማራ የሚያሸንፍ መሆኑ ቁርጥ እየሆነ ሲመጣ በዐማራ በኩል ታዝለው 4ኪሎ የሚናፍቁም የትየለሌ ናቸው። የከሰረ ጡረተኛ ዳያስጶራ ሁሉ ቀሪ ዘመኑን በፋኖ ታዝሎ አንቱ፣ የተከበሩ ምኒስትር መባልን ፈልጎም ቋምጧል። ከአሁን ስንት ሕንፃ እንደሚሠራ ወስኖ ፕላንና ዲዛይን አሠርቶ የተቀመጠ የኡበር ሹፌር ሁላ አለ። እነ ወይዘሮ እገሊትም በቀረቡት ፋኖ ልክ ሙቀት እየተሰማቸው አዛዥ ናዛዥ የሆኑ ሁላ ቁጥር ስፍር የላቸውም።

"…ከጋዜጠኝነት ባሻገር የትግል ማኒፌስቶ አዘጋጅተው ፋኖን ለመጠምዘዝ የሚሞክሩ ምስኪኖች ሁላም አይቻለሁ። የፋኖ ትግል ከባድ ነው። አትችሉትም። የፋኖ ትግል የእግዚአብሔር ቁጣ ነው። ስዩም ተሾመ ተበሳጭቶ አረፋ ሲደፍቅ ሳየው አቢይ አሕመድ እንደተዠለጠ እና እየተነፋረቀ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ። አሁን በዚሁ ከገገሙ። እኔንም ቢሆን በመሃላቸው አድርገው መነጋገር አቁመው በራሳቸው መንገድ፣ ባህል፣ ሃይማኖት መወያየት ከጀመሩ በዐማራ በኩል ነፋስ አይገባም።

"…በትግሉ የቆዩት አረጋውያኑ ለወጣቶቹም ዕድል እየሰጡ፣ እነሱ እንደበሬ፣ ወጣቶቹን እንደወይፈን አንድ ላይ አጣምሮ ማረስ ከጀመሩ ትግሉ ከዳር ይደርሳል። ከህወሓት ጋር ሳይሆን ከትግሬ ከሕዝቡ ጋርም ውይይት ቢጀመር ኦሮሙማው አይቀልድባቸውም ነበር። ብአዴኖችንም ቢሆን ሁሉንም ከመግፋት የሚመከረውን በቄስ በሼህ እየመከሩ የትግላቸው አጋር ቢያደርጉም መልካም ነው። አልመለስ ያለውን ደግሞ ያው መኮርኮም ተፈጥሮአዊ ነው። ከኦሮሞም ሆነ ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ቢገፉአቸውም ዐማሮቹ ግን በቀደመ ፍቅራቸውና አቃፊነታቸው መቀጠል። መከላከያ ሠራዊቱ ሲማረክ በፍቅር መያዙን አጠንክረው መያዙ ያተርፉበታል።

"…በተረፈ በዐማራ ትግል ላይ መሽንክ ለመሆን የምትሞክር ዐማራ ነኝ ባይም ብትሆን እኔ የሀረርጌው ቆቱ መራታው ዘመዴ፣ የሥላሴ ባርያ የድንግል አሽከር፣ የምሥራቁ ሰው ባለማዕተቡ የተዋሕዶ ልጅ አልፋታህም። የፈለግከውን በለኝ አልፋታህም። ጩህ እሪ በል። ቀውጠው ምንም አባክ አታመጣም። አልቅስ። መጪው ጊዜ የዐማራ ነው። ዐማራ የሚመራት ኢትዮጵያ እውን ትሆናለች። ፍቅር፣ ፍትሕ በምድሪቱ ይነግሳል። ክልል ይፈርሳል። ድንበር ከጎረቤት ሀገር ጋር ብቻ ነው የሚሰመረው። ደም አፍሳሾች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ ዘራፊ ወንበዴዎች በሙሉ በፍትሕ ይዳኛሉ። የጃቸውንም ያገኛሉ። ኢትዮጵያዊ የሆነ በሙሉ ልቡ ከፈቀደበት ሥፍራ ሁሉ ለጤናው ተስማሚ ከሆነ ስፍራ ሂዶ የሚኖርበት፣ ሀብት አፍርቶ የሚኖርበት የተረጋጋ ሀገር ይፈጠራል። ለዚህም ተስፋ ሳልቆርጥ እደክማለሁ።

"…አንተ ቁጭ ብለህ አውራ፣ ፎግር፣ ፎትት፣ ተርብ፣ ደስኩር፣ እኔ ዘመዴ ግን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር በሟሟቅ ላይ እገኛለሁ። አለቀ።

• ድል ለዐማራው ፋኖ…!
• ለተገፋው ለዐማራው ሕዝብ…!

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ…!