እድሜህ በጨመረ ቁጥር ለዚህ ምድረ ዓለም ይህን ያህል መጨነቅ እንደማያስፈልግ ትገነዘባለህ። ችግሮች ይሄዱና መልካቸውን ቀይረው ይመጣሉ። የነበሩ በርካታ ሳቆች ይሞቱና የተለዩ ሳቆች ይወለዳሉ። በዚህ የህይወት ትግል ውስጥ ዝንተዓለሙን በሳቅ ብቻ የሚኖር ባለፀጋ አታገኝም። እድሜልኩን በችግሮች ማዕበል እየታመሰ የሚኖር ሰውም የለም። ህይወት መኖር ነው። ሳቁንም መከራውንም እየታገሉ መኖር ነው። ሌላ ፍልስፍና የለውም። 320 viewsᏃᗩᏦᏆᖇ, 12:22