የምስጋና በዓል ጥሪ ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የኃያላን መቅደስ ቤተ ክርስትያን ከእግዚአብሔር በተቀበለችው ተልዕኮ መሠረት በቃሉ እና በመንፈሱ የታጠቁ ኃያላንን ማፍራት የጀመረችበት ሰባተኛ ዓመት የምሥረታ በዓል የፊታችን ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓም በታላቅ ድምቀት ይከበራል። በዓሉ የሚከበረው እግዚአብሔር ለራዕዩ ማረፊያ ይሆን ዘንድ በሰጠን ሰፊ ቦታ ላይ መሆኑ ምስጋናችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል። በመሆኑም በተዘጋጀው የምስጋና ድግስ ላይ የራዕዩ ቤተሰቦች፣ ከራዕዩ የተጠቀማችሁ፣ በእግዚአብሔር መንግሥት አብሮ ሠራተኞች እንዲሁም ደስ ካላቸው ጋር ደስ የሚላችሁ ቅዱሳን በሙሉ እንድታደሙ በጌታ ፍቅር ተጋብዛችኋል። ጧት- 3፡00 -7:00 ከስአት 10:00-2:00 አድራሻ - ከኃያት አደባባይ ወደ 72 በሚወስደው መንገድ ዙሪያሽ ሞል ፊት ለፊት 1.1K views09:22