2020-12-22 14:25:16
“አድራጊ” ሲባል “ወንዳወንድ” ፣ ተደራጊ ሲባል ደግሞ “ሴታሴት” ናቸው ብለን የምንፈርጃቸው ሰዎች ወይም ማንነቶች ቶሎ ወደ ጭንቅላታችን የሚመጡ ብዙዎች ነን፡፡ ነገር ግን ይህን ስል ውስጣዊ ስሜታችን የሚነግረንን ነገርን በመዘንጋት አይደለም፡፡ በፍላጎታችን ወይም መርጠን እነዚህን ነገሮች እንድንባል ወይም በዛ መንገድ እንድንታይ የምንፈልግን ሰዎችም መርሳት የለብንም፡፡ ይህም ስሜት ፣ ፈቃድ ፣ ፍላጎት ወይም ምርጫ ወደምንለው ነገር ያመጣናል፡፡
ወሲባዊ ሚና የፍላጎት ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅርም ሆነ ጊዜያዊ የወሲብ ስሜት የሚኖረን አንድን ሰው ለመጀመሪያ ጊዜ ባየንበት አፍታ ወይም ደግሞ በደንብ ስንላመድ እንደመሆኑ ፣ እነዚህ ስሜቶች በዛ ሰው ወሲባዊ ሚና ላይ የተመረኮዙ አይሆኑም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ በማንነቱ ተስበናልና፡፡ ከዛ ዘለል ሲል ነው ሚናችንን የምንተዋወቀው፡፡
ከምንም በፊት ሰዎች ነን ፣ ከዛም በማህበረሰባችን የተገፋን ሰዎች ፣ ከዛ ባለፈ አንድ ዓይነት ፆታዊ ተስህቦ ኖሮን ፣ አንድ ዓይነት ኑሮ እየኖርን ፣ በአንድ ስም እየተጠራን ሌሎች ተጨማሪ የሚከፋፍሉ ወይም ደግሞ ከፍ እና ዝቅ አድርገው የሚያስተያዩንን ክፍፍሎች መፍጠር የለብንም፡፡
ይሁን፡ ስያሜዎቻችን ይኑሩ፡ ነገር ግን ከጀርባቸው ያለውን ትርጓሜ ማስተካከል ያሻል፡፡
በዚህ ግለሰባዊ ነፃነት በሚሰበክበት ዘመን ፣ ዓለም ወሲባዊም ሆነ ሌላ ፍላጎቶቹን በፈለገው መንገድ ፣ እሱን በሚያስደስተው ሁናቴ መግለፅን ባህሉ እያደረገ በመጣበት ዘመን ኋላ ቀሩን እና አንዱን የበላይ አንዱን የበታች አድርጎ የሚያስብ ትውልድ ሊኖረን አይገባም፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ በጣም ብዙ ልንኮራበት እና ልንታይበት እንዲሁም ልናከብረው የሚገባቸው ባህሎች እና ትውፊቶች ቢኖሯትም ልንቃወመው እና በተቻለን ሁሉ ለሚቀጥለው ትውልድ እንዳይተላለፉ የምንታገልላቸው መጥፎ እና የአንድን ሰው ሰብዓዊ መብት የሚገፍፉ ስርዓቶች እና ህግጋቶች አሏት፡፡
በእኛ (በዜጎች) ላይ የሚሰነዘረውን ጥላቻ ፣ ስድብ እና ማንቋሸሽ በብቃት ልንቋቋም እና ልንታገል የምንችለው እርስ በእርሳችን በእኩልነት ስንተያይ እና ስንከባበር ብቻ ነው፡፡
ሁሉም እንደየስሜቱ ይተግብር ፣ ሁሉም እንደ ፍላጎቱ ይከበር።
ቸር ያውለን
ቤን ዶሚነስ
የዜግነት ክብር
4.1K views11:25