Get Mystery Box with random crypto!

የነፍሴ ጥያቄዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ yenebsetiyakewoch — የነፍሴ ጥያቄዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ yenebsetiyakewoch — የነፍሴ ጥያቄዎች
የሰርጥ አድራሻ: @yenebsetiyakewoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.30K
የሰርጥ መግለጫ

✋እንኩዋን ወደ ቻናላችን በሰላም መጡ
በዚ ቻናል ውስጥ ከእሰላም ወገኖቻችን የሚነሱ ጥያቄዎችን እንመልሳለን እንተነትናለን እባክዎን ልቦን ክፍት አድርገው ይከታተሉ👍
ለአስተያየት ለጥያቄ ለምክር @yenebsebot ይጠቀሙ
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
አስተያየት ካለ ያሳውቁን እንጂ Live ብለው ማግኘት ያለቦትን እንዳያጡ!!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-08 11:04:17 ከሆነ ቦታ ወደ ሆነ ቦታ እየሄድኩ የተከፈተው ለሙሀመድ የተዘፈነው ዘፈን ደስ ሲል። አሁን አሁን የምታወጧቸው ነሺዳዎች ግን ሙሀመድን ከአላህ እኩል ያደረጉ ይመስላሉ ስለ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ስናወራ መቃወምን ማቆም ያለባቹ ይመስለኛል ምክንያቱም እናንተም ሁለት አምላክ ወደ ማምለክ እየሄዳቹ ነው ሙሀመድን እና አላህን፤የኛው አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ብለን አንድ አምላክ ነው የምንለው አንድ አምላክ አሀዱ አምላክ ነው። የናንተው ሁለት አምላክ መሰለኝ አላህ አንደኛው አምላክ ከአላህ ያነሰው ሁለተኛው አምላክ ሙሀመድ።

@yenebsetiyakewoch
2.0K views08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-27 11:52:22 የ tiktok አብዱሎች የሚጠይቁትን ጥያቄ በ tiktok ለመመለስ ስል ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት tiktok account ከፈትኩ እና እስኪ ፈቃዳቹ ከሆነ እየገባቹ follow አድርጉ

tiktok.com/@ewenetn

ይቅር በዚሁ ይበቃል የምትሉ እቺን
በዛም ያስፈልጋል ምትሉ እቺን እየነካቹ ሄዳቹም follow አድርጉ
2.5K views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-27 11:15:39 "ለምንድነው የምትፆመው?"

ይሄን ጥያቄ የሚጠይቁ ሰዎች አሉ፤ይህን ጥያቄ ክርስትያን ነኝ ከሚል ሰው መስማት ያሳዝናል።

ለምንድነው ምፆመው? ሞት እየነገሰ ሰው እንዴት ይህን ጥያቄ የመጠየቅን ድፍረት ሊያገኝ ይችላል? ወደ ግራ እና ወደቀኝ ዞር ዞር ብለን እንመልከት እስኪ ምን ይታይሀል? ምንስ ይታይሻል? በሽታ፣ሱሰኝነት፣ኑፋቄ...ወደልጆቻችሁ ክፍል ብትገቡ ምን ታያላቹ? ብትቀርቡዋቸው አብራቹ ብትቀመጡ እና ውስጣቸውን ብትረዱ ያሉበትን ሁኔታ የሚያጨሱትን የሚያዩትን ብትመለከቱ ደምስሮቻቸው ላይ ምን ሰክተው በምን እንደሚጦዙ ጓደኞቻቸው እነማን እንደሆኑ ብታውቁ፤TV ከፍታቹ ብትመለከቱ ራሳችሁን ብታደምጡ የምትሰሙት ጦርነት የምታዩት ሴሰኝነት የምትረግጡት መሬት በደም የራሰ ተስፋ የሚያስቆርጥ እንደሆነ ይገባቹዋል።

ከዛ ለምን መፆም እንዳለብን ይገለጥላቹዋል ለምን እንደምንፆም ይገባቹዋል። ተስፋ ላለመቁረጥ ስንል እንፆማለን፤በንፋስ የሚሰበር ሸንበቆ ላለመሆን ስንል እንፆማለን።

አለማዊ ለስላሳ ልብስን አንፈልግ!
በቁም ሬሳዎች የተሞሉ ትላልቅ ቤቶችን አንፈልግ!
ሰይጣናዊ ዝሙታዊ ጭፈራዎችን አንፈልግ!
ወደ መጥምቁ ዮሀንስ የንስሀ ጥሪ እንመለስ!
ሊመጣ ያለውን በመላእክት ታጅቦ የሚመጣውን ንጉሱን ለመቀበል እንዘጋጅ!
የምንፆመውም ለዛ ነው!
ከመንግስቱ እንዳንጎድል ነው በንስሀ የምንኖረው!
መስቀሉን እና ስቃዩን እናስብ ለአለም ችግር የኛ ፆም እና ስግደት ፀሎታችን መፍትሄ አለው ለዛም እንፆማለን!

አንድ አባት የመለሱትን መልስ ከራሴ ጋር አዋህጄ ፃፍኩላቹ ፆማችን መፍትሄ አለው!
share join share
@yenebsetiyakewoch
@yenebsetiyakewoch
2.1K viewsedited  08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 09:26:06 በእንተ ቆላስይስ 1፥16

የአይሁዳውያን መሠረተ እምነት ከሆኑት ዶግማዎች መካከል በቀዳሚነት የሚሰለፈው የእግዚአብሔር ብቸኛ ፈጣሪነት ነው። የብሉይ ኪዳንም የመጀመሪያ ክፍል የእግዚአብሔርን አስገኚነት በመናገር የሚጀምረው በዚህ አግባብ ነው(ዘፍ 1፥1)። ኢሳይያስም በትንቢቱ የዘፍጥረት 1፥1 ምንባብ በሚያጸና መልኩ ይኽን ይላል፣ “ብቻዬን ሰማያትን የዘረጋሁ፣ ምድርን ያንጣለልሁ፣ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤”(ኢሳ. 44፡24)። ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ ደግሞ ሁሉም ነገር የተፈጠረው በእግዚአብሔር ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ እንደሆነ ንዋይ ሕሩይ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ያረጋግጥልናል፦

“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለ ሥልጣናት፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16

ከላይ ባለው በጥቅሱ ውስጥ ሐዋርያው “ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል”(ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη τὰ πάντα ) ይለናል፡፡ ይኸውም በእግዚአብሔር አብ ልጅ ዓለማት መፈጠሩን እናም ልጁ ኢየሱስ ልክ እንደ አባቱ የአምላክነት ተግባርን ይከውን እንደነበር ያስገነዝበናል። ሆኖም የክርስቶስን አምላክነት የማይቀበሉ ወገኖች በሚከተለው ሙግት በቆላስይስ 1፥16 የተጠቀሰውን የጌታችንን ፈጣሪነት ለማስተባበል ይሞክራሉ። ይኸውም፤ “' ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል' የሚለው አዲስ ፍጥረትን የሚያመለክት እንጂ ክርስቶስ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣቱን የሚያመለክት አይደለም” የሚል ነው።

ከላይ የሚገኘው ሙግት ቢያንስ ሶስት መሠረታዊ ነጥቦችን ያላገናዘበ ነው። ይኸውም፤

1ኛ. መና*ቃን ይህ ትርጓሜያቸው የቋንቋ (Linguistic approach) ድጋፍን መሠረት ያላደረገ ነው። ምክንያቱም ἐκτίσθη “ኤክቲስቴ” የሚለው ቃል ቊማዊ ፍጥረትን እንጂ በፍጹም ተምሳሌታዊ ገለጻን ለማመልከት ግልጋሎት ላይ አይውልም[1]። ይህ ማለት የመና*ቃን ሙግት ከጅምሩ ወንዝ የማያሻግር ሆኖ ይቀራል ማለት ነው።

2ኛ.ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ 11፥36 የአብ ፈጣሪነትን የገለጠበትን ምንባብ ከቆላስያስ 1፥16 ጋር በትይዩ ተመልከት፤

አብ፦
“#ሁሉም(τὰ πάντα) ከእርሱ፣ #በእርሱ(δι’ αὐτοῦ)፣ #ለእርሱ(εἰς αὐτὸν) ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— ሮሜ 11፥36 (አዲሱ መ.ት)

ወልድ፦
“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለ ሥልጣናት፣ #ሁሉም(τὰ πάντα) ነገር #በእርሱና(δι’ αὐτοῦ) #ለእርሱ(εἰς αὐτὸν) ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16 (አዲሱ መ.ት)

በሁለቱም ጥቅሶች ውስጥ “ሁሉም” (τὰ πάντα “ታ ፓንታ”) ፤ “በእርሱ” ( δι’ αὐτοῦ ዲ አውቱ)፤ “ለእርሱ” (εἰς αὐτὸν ሔይስ አውቶን)፤ የሚሉትን ቃላቶችን ተጠቅሞአል። ስለዚህ ቆላስይስ 1፥16 ላይ የወልድን ፈጣሪነት አያሳይም ካሉን፣ በተመሣሣይ የሮሜ 11፥36 ምንባብም እንዲሁ የአብን ፈጣሪነት አያሳይም ብለው መደምደም ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ሐዋርያው ለሁለቱም አካላት ተመሣሣይ ሰዋስዋዊ ውቅር ተጠቅሞአልና።

3ኛ.የመና*ቃን ችግር ሐዋርያው በክርስቶስ ተፈጠሩ የሚለን በሰማይ የሚኖሩ ገዢዎች እና ሥልጣናትን መሆኑን አለማስተዋል ነው።

“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት፣ ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ *ገዦች*(ἄρχαι) ቢሆኑ ወይም *ባለ ሥልጣናት*(ἐξουσίαι)፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16

ጳውሎስ በሌላ ጽሑፉ ላይ ክርስቲያኖችን የሚዋጉ ዓመፀኛ መናፍስት ፍጥረታትን በሚመለከት “ገዦች ” እና “ሥልጣናት” የሚሉትን ቃላት ተጠቅሟል።

“ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከዚህ ከጨለማ ዓለም *ገዦች*(τὰς ἀρχάς)፣ *ከሥልጣናትና*(τὰς ἐξουσίας) ከኀይላት እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው።”
— ኤፌሶን 6፥12 (አዲሱ መ.ት)

ይኽም ማለት ኢየሱስ ቅዱሳን ሆነ እርኩሳን መናፍስትን የፈጠረ አምላክ መሆኑን በግልጽ ያመለክታል።በአጠቃላይ ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስን የበላይነት፣ አድራጊ ፈጣሪ መሆኑን በግልፅ እየተረከልን ነው። እርሱ ተራ መልአክ ወይም ተራ ሰው አይደለም፣ ነገር ግን ከሁሉም በላይ የሆነ፣ ሊመለክ የሚገባው ፈጣሪ ነው። ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘለዓለም ክብር ይሁን! የሚያመልከው አሜን ይላል።

[1] መጽሐፈ ጥበብ 1፥14፤ 10፥1፤ 11፥18፤ ዘዳግም 4፥32፤ ዘፍጥረት 6፥7; ሲራክ 24፥9፣ ሲራክ 15፥14፤ መጽሐፈ ኢዮብ 13፥18፤1 ቆሮንቶስ 11፥9፤ ኤፌሶን 3፥9፤ ሮሜ 1፥25፤ ራእይ 10፥6፣ ራእ 14፥7

(በወንድም ሚናስ)

Share join share
@yenebsetiyakewoch
@yenebsetiyakewoch
3.4K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-02 13:30:24 ብዙ ሙስሊሞች ክርስትናን ዲዳት እና ዛኪረ በነገሩዋቸው ልክ ነው የሚያውቁት!

መፅሀፍ ቅዱስን ማንበብ ማለት የዲዳት እና የዛኪርን የቆዩ ተመልሰው ያለፉ ጥያቄዎችን እንደአዲስ ማስጮህ ይመስላቸዋል።

ተወዳጆች ሆይ መፅሀፍ ቅዱስን በሰዎች ወይም በእስልምና መነፅር ከምታነቡ ባታነቡ ይሻላችዋል ይልቁንስ እውነትን ከፈለክ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ በትክክለኛው መንገድ በአውዱ መሰረት አንብበው እመነኝ የዛኔ ክርስትና ትገለጥልሀለች።
2.7K viewsedited  10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-29 10:17:18
እንዲ አይነት ወጣቶችን አበረታቱት ጥቂት ለማለት ያክል..

ዘሌዋውያን አብይ ሀሳቡን ቅድስናን አድርጎ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በአሮን ልጆች የክህነት አገልግሎት የሚካሄደውን እና በሌዋውያን የሚታዘዘውን ስርአት የሚያሳይ ነው።

ልጅቱዋ ወደ ምትለው ዘሌዋውናን 21 ስንመጣ ወንድሜ ጥሩ አድርጎ መልሶላታል ተባረክ። አንድ ጥቅስ ይዛቹ አትጋልቡ ስለማን ስለምንድነው ክፍሉ ሚያወራው ብላቹ ጠይቁ በመገናኛው ድንኩዋን መስዋእቱም ሰዊውም ንፁህ መሆን ይጠበቅባቸዋል። ካህን አልሆኑም ማለት ከእግዚያብሄር ህዝብነት ጎደሉ ተቆረጡ ተካዱ ማለት አይደለም ካዳቸው ያልሻቸውን ሰዎች እግዜርም ህዝቤ ብሎ የጠራቸው በድንቅ ተአምራት ከግብፅ ባርነት አስወጥቶ የመራቸው እሱ ነው ይህን ስርአት የሰጠው!

"መፅሀፍ ቅዱስ የእግዝያብሄር ቃል ነው ወይ?" የሚለውን "የተበረዘው መፅሀፍ ቅዱስ ወይስ ቁርአን?" በሚል ርእስ በተከታታይ ክፍሎች ለቀን ነበር ጋብዙልኝማ።

@yenebsetiyakewoch
@yenebsetiyakewoch
3.0K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 09:39:45 ትልቅ ማን ነው?



(ማቴ 11÷9-11)

ለማኙ የባለጠጋውን ቤት አልፎ የድሃዋ በር ላይ ቆሞ፡- ‹‹በእንተ ማርያም›› እያለ ይለምናል፡፡ ድሃዋም፡- ‹‹ይህን ትልቅ ቤት አልፈህ እንዴት እኔ በር ላይ ትለምናለህ?›› ይሉታል፡፡ ለማኙም፡- ‹‹አይ እሜቴ ትልቁ ቤት ትልቅ ሰው የለበትም›› አላቸው ይባላል፡፡ ድህነትን እንደ አመል በመቊጠር የባለጠጎችን ቤት ስናይ የደህና ሰው ቤት ነው እንላለን፡፡ የሰውዬውን ትልቅነት በቤቱ እንመዝነዋለን፡፡ ቤት የትልቅነት መለኪያ ሆኗል፡፡

አለቃ ገብረ ሃና እንደነገሩ ለብሰው ወደ ተጠሩበት ድግስ ይሄዳሉ፡፡ በሩ ላይ የቆመው ዘብም አላስገባም ብሎ ይመልሳቸዋል፡፡ እርሳቸውም በልብሳቸው እንደ ተመዘኑ ገብቷቸው ደህና ልብስ ለብሰው ተመልሰው ቢመጡ እጅ ነሥቶ አስገባቸው፡፡ እርሳቸውም ከእንጀራው ላይ ወጡን እያነሡ ልብሳቸውን መለቅለቅ ጀመሩ፡፡ ሰዎቹም ምነው አለቃ ምን ነካዎት? ቢሏቸው፡- ‹‹የተጠራሁት እኔ ሳልሆን ልብሴ ነው›› አሉ ይባላል፡፡ አለባበስ የትልቅነት መለኪያ ሆኗል፡፡ ከአባባሉም፡- ‹‹ኖር ለልብሱ›› ነው፡፡ እኛም ሰዎች ሲለብሱና ሳይለብሱ የማንቆጣጠረው ማንነታችን ሁለት ሰው ያደርገናል፡፡ ውሾች ሱፍ የለበሰ ላይ አይጮኹም፣ ለማኙን ደግሞ ወርረው ያጣድፉታል፡፡ ይህ ነገር ምንድነው ብዬ አንድ ወዳጄን ብጠይቀው፡- ‹‹ፍርፋሪያቸውን የሚወስድባቸው ስለሚመስላቸው ነው›› ብሎኛል፡፡ እኔስ ከእኛ ተምረው ይመስለኝ ነበር፡፡

የሚያስደስተን የሚበቃን ኑሮ ስላለን ሳይሆን ከሌሎች በመብለጣችን ነው፡፡ ትልቅነት ትልቅ መከራ እንዳለው በቃላት አይገባንም፡፡ ለትልቅነት መሥራትና ትልቅ ሥራ መሥራት ይለያያሉ፡፡ ለትልቅነት የሚሠሩ በሌሎች ላይ ይራመዳሉ፡፡ ትልቅ ሥራ የሚሠራ ግን መሥዋዕት ይሆናሉ፡፡ ብዙ ትልልቅ ሰዎች ያልበደሉ ልጆቻቸው እንኳ አገር የለሽ ሆነዋል፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጆችና የልጅ ልጆች ምንድነው በደላቸው? ትልቅ ኑሮ ትልቅ ጉድ እንዳለው እግዚአብሔር ብቻ ያውቃል፡፡ በየመንደሩ ይዞር የነበረው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በየቤቱ ያለው ድብቅ ልቅሶ ይሰማው ነበር፡፡ ያለ ልቅሶ የማይኖሩ ቤቶች እንደሌሉ እርሱ ብቻ ያውቅ ነበር፡፡

ጌታ ኢየሱስ ስለ እነ እስክንድር ወይም ስለ እነ ኔሮን ታላቅነት አልተናገረም፡፡ ስለ ዮሐንስና ጴጥሮስም የትልቅነት ክርክር ዕጣ አልጣለም፡፡ ሕፃን አምጥቶ ትልቅ ይህ መሆኑን ነገራቸው (ማቴ. 18÷1-4)፡፡ ሕጻን ትንሽ መሆኑን ሁሉም ያምናሉ፡፡ የተከበሩ ሰዎች ሕጻናትን ያከብራሉ፡፡ የዛሬው ሳይሆን የወደፊቱ ማንነቱ እየታያቸው ስፍራ ይሰጡታል፡፡ ሰው እንደ አሁኑ ሆኖ አይቀርም፡፡ የሕጻን ትልቅነቱ ስህተቱን ለመቀበል አያፍርም፣ ፍቅርን ይሰጣል እንጂ ለብድር ኑሮ አይኖርም፣ መቀበል ይችላል እንጂ አይግደረደርም፣ ራሱን ዝቅ ያደርጋል፣ ለማወቅ ይጥራል፣ ያልገባውን አስመስሎ ማለፍ አይችልም፣ በደልን በቶሎ ይረሳል፣ ምን እበላለሁ? ምን እለብሳለሁ? የማይል መንፈሳዊ ነው፡፡ የትልቅነት መስፈርቱ እንደ ሕጻናት መሆን ነው፡፡

ትልቅ ለመሆን በፖለቲካ ውስጥ ብዙዎች ይሽሎኮለካሉ፡፡ ዝነኛ ለመሆን ከሰማይ ጠቀስ ፎቅና ከታወቁ ድልድዮች ብዙዎች ራሳቸውን ይጥላሉ፡፡ እስከ ዛሬ ትልቅነት ያደክም ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ይገድላል፡፡ ግን ለትልቅነት ብለው የሠሩት ትልቅ ያደርጋል? ትልቅነት እኛ እንፈልገዋለን ወይስ ይመጣል?

ዮሐንስ መጥምቅ ትልቅ ሰው እንደ ሆነ የመሰከረው ጌታችን ነው (ማቴ. 11÷9-11)፡፡ ጌታችን ዮሐንስን ትልቅ ያለው የዓለምን መመዘኛ ፍጹም በመጣል ነው፡፡ ዓለም ትልቅ ለማለት አራት ነገሮች እንደሚያስፈልጉ ታምናለች፡፡

1. ቤት፡- ቤቱን ብቻ በማየት ይህ የትልቅ ሰው ቤት ነው እንላለን፡፡ በመላው ዓለም የተሟላ ቤት ያላቸው ትልቅ ይባላሉ፡፡ ዮሐንስ ግን ቤት ያልነበረው በበረሃ የሚኖር ሰው ነበር (ማቴ. 3÷1-2)

2. ልብስ፡- ቀድመን የምናየው ሰውዬውን ሳይሆን ልብሱን ነው፡፡ ፕሮቶኮሉን ያልጠበቀ ሰው የማይገባባቸውና የማይሠራባቸው ስፍራዎች አሉ፡፡ ፖሊስ ቀድሞ የሚያነሣው ደህና ለብሶ የወደቀውን ነው፡፡ ዮሐንስ ግን ልብሱ የግመል ጠጉር፣ መታጠቂያውም ጠፈር ነበር (ማር. 1÷6)፡፡

3. ምግብ፡- ሁላችንም ቆመን ብንሄድም ለየት ያለ ምግቦችን በውድ ዋጋ፣ በደረጃ የሚመገቡ ሰዎች ትልቅ ሰዎች ይባላሉ፡፡ የሕንድ ባለጠጋ ለምሳ ለንደን ይሄዳል ይባላል፡፡ የታወቁ ወጥ ቤቶች የሠሩትም ሆነ ሌላው ምግብ ክብሩ ከጉሮሮ እስኪያልፍ ነው፡፡ ዮሐንስ ግን ምግቡ አንበጣና የበረሃ ማር ነበር (ማር. 1÷6)፡፡

4. የንግግር ችሎታ፡- ዛሬ የዓለምን የሥልጣን በትር የጨበጡ ሰዎች በንግግር ችሎታቸው የታወቁና ጥሩ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ዮሐንስ ግን የማንንም ወዳጅነት ሳይፈልግ በደልን የሚያጋልጥ ነበር (ሉቃ. 3÷7)፡፡ ግን ትልቅ ነበር፡፡

ታድያ ትልቅ ማን ነው

ከድንግል ማርያም ልጆች ቻናል የተወሰደ

@yenebsetiyakewoch
@yenebsetiyakewoch
3.0K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-26 11:56:22 ሙሀመድ ነብይ ሊባል የሚችለው ከፊት ለፊቱ ሀሰተኛ የሚል ቅፅል ካለው ብቻ ነው !!
2.5K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-25 08:39:53 ሰላም ለእናንተ ይሁን ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህንን የምታነቡ በሙሉ የእግዚያብሔር ሰላም በሁላችሁ ላይ ይሁን


" በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።"
(የማቴዎስ ወንጌል 16:18)

ቤተ ክርስትያንን የገሀነብ ደጆች አይችሉዋትም የገሀነብ ደጆችም ትግልን ይታገላሉ ቤተክርስትያንም ታሸንፋለች! ቤተክርስትያንን ከፖለቲካ ጋር የምታያይዙ የከበረውን ከቀለለው ባታዋድዱ እላለው እሱዋ ከፖለቲካ በላይ ነችና!
2.8K views05:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-29 09:56:51 ቻናሉን በቅርብ ቀን አስተካክለን በአዲስ መልክ እንማማራለን እስከዛው በማስታወቂያ እንዳትሰለቹ ካሁን በፊት የነበረውን bot እየተቆጣጠርነው ስላላይደለ አዲስ bot እናሳውቃችዃለን። ቻናሉንም በአዲስ መልክ ምንጀምረው ይሆናል እስከዛው መልካም ገዜ


በምድር ላይ የምኩራራበት ትልቁ ንብረቴ ክርስትናዬ ብቻ ነው ክርስትና መስቀሉን መከራውን በመሸከም ከሱ ጋር የምናደርገው ጉዞ ነው
12.4K viewsedited  06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ