Get Mystery Box with random crypto!

ማማት ካልሰለቸሽ... °°°°°°°°°°°°°°°°°° ጸጉሩን አጎፍሮ፥ ጺሙን አንጨብሮ፥ በነተበ ሹ | የግጥም ህይወት

ማማት ካልሰለቸሽ...
°°°°°°°°°°°°°°°°°°

ጸጉሩን አጎፍሮ፥
ጺሙን አንጨብሮ፥
በነተበ ሹራብ ስካርፑን ጠምጥሞ፣
በብርሃን ዘመን ይመጣል ፀልሞ፤
ይኼ የፍካት ፀር . . .
ውበትን ቆልምሞ።

በመጽሐፍ ገጾች ላይ ዐይኖቹን ወሽቆ፣
የሌለሁኝ ያህል ዋጋ ክብሬን ፍቆ፤
ከምንም ሳይቆጥረኝ ጥሎኝ ይከንፋል፣
መኖሬን ደርምሶ ዓለሙን ያስፋፋል፤
አትስሙ የሱን ጉድ . . .
እጅግ ይከረፋል።

ጨለምተኛ ነው
ከራሱ በስተቀር አያፈቅርም ሌላ፣
ገፍትሮ ይጥላል
ማስደፈር አይሻም የልብ አጥሩን ኬላ።
ስንት ጊዜ አንኳኳሁ ቆፈቆፍኩ በብርቱ፣
ተከርችሞ ቀርቷል መክፈቻ ጉጠቱ።

የሰው ስቃይ፣ ሕመም
ቆስቁሶ እየሰማ . . . ድርሰቱን ያደራል፣
የራሱን በደል ግን ከፍኖ ይቀብራል።
መናገር አይሻም ማዳፈን ነው ወልፉ፣
እንግልት ብርታቱን
ሰሚ እንዳይኖረው ዘግቶታል በቁልፉ።
.
.
ምናምን እያልሽ . . . ታሚኛለሽ አሉ!!
:
:
ግድ የለም ቦጭቂኝ!!
ግድ የለም ሸርድጂኝ!!
ግን ደግሞ እወቂ፥
ሐሜት እና አሽሙር አይጥለኝም ጠልፎ፣
ከጽልመት ገላ ላይ
ፈልቅቄ መዛለሁ የብርሃን ወጨፎ።

ዝለፊኝ አብዝተሽ!!
ውቀሽኝ አጥብቀሽ!!
ግን ደግሞ ተረጂ፥
ላፈቀረ ሁሉ ልብ አይከፈትም፣
ማጣት ብቻ አይደለም
ልኩን ካላወቀ ያስከፋል ማግኘትም።

እሚኝ አይደንቀኝም!!
ስደቢኝ አላዝንም!!
ግን ደግሞ እመኚ፥
ህይወቴ ተነጥፏል ከድርሰት ጫንቃ ላይ፣
ማንበብ እና መጻፍ
ሀሴት ያለብሰኛል ካንቺ ግብዣ በላይ።
.
:

#ኤልዳን

@yegtm_hywet
@yegtm_hywet