Get Mystery Box with random crypto!

😷 FKR en GETM💕💕

የቴሌግራም ቻናል አርማ yefkrinegri — 😷 FKR en GETM💕💕 F
የቴሌግራም ቻናል አርማ yefkrinegri — 😷 FKR en GETM💕💕
የሰርጥ አድራሻ: @yefkrinegri
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 923
የሰርጥ መግለጫ

@yen tewlde❤️✅ህይወት ትቀጥላለች አንዱን ከሌላው ድርና ማግ እያደረገች።
❤️✅ውድ የቻናሉ ቤተሰቦች ፍቅርን እንዝራ..ፍቅርን እንስበክ..ፍቅርን እናቀንቅን።.....
❤️✅ያልተነበቡ ድርሰቶችን..ግጥሞችን..ታሪኮችንና ሌሎች መጻጽፎችን ያገኙበታል። Join ብለው ይቋደሱ።
.
.
.
.
ለማስታወቂያ ስራዎች [For promotion] @yefkrinegri

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-20 22:09:26 "አብሮት ማሳደጊያ ያደገ ጓደኛው የነበረ ሰው እንደነበር ? ከሀገር ውጪ ነበር መሰለኝ ለእረፍት በመጣበት ነው የተገደለው።"

"ገደለው?" አልኩኝ ሳላስበው።

"ምነው ታውቂዋለሽ?"

"አዎ! ማለቴ አላውቀውም ግን አሸናፊ ሲያወራ ሰምቻለሁ:: እርግጠኛ ነኝ እሱ ነው!! " አልኩኝ ደሜ ቀዝቅዞ

ይቀጥላል እኮ ....
266 views @du , 19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 "ባንቺ ሁኔታ ስለምግብ ማውራት ቅንጦት ስለመሰለኝ እንጂ ቁርስ እንኳን ሳንበላ ነውኮ ጠዋት የወጣነው!" አለኝ ግሩም!

ይቀጥላል ......

እኔ የምለው ዛሬኮ የአባት ሀገር ገና ነው!! በበዓል ግን ቁጭ ብዬ እንደፃፍኩላችሁ ታውቃላችሁ? ያው መውደዴን እንድታውቁት ታክል ነው። በዓሉ ለሚመለከታችሁ። ያማረ በዓል ከምትወዷቸው ጋር ይሁንላችሁ።
252 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 "እ? አዎ አይ እርግጠኛ ነኝ! ችግር የለውም!" አልኩኝ ደረቴን በርቅሳ ልትወጣ ይመስል የምትደልቅ ልቤን እንዳያዩብኝ ልብሴን እየነካካሁ። ምንም ባልናገርም ፊቱን ማየት እንደሞት እንዳስፈራኝ ከሁኔታዬ ገብቷቸዋል።

አባትየው ለአንደኛው ፖሊስ ሲያስረዳ ሲጨቃጨቁ አጠገባቸው ሆኜ እንደእሩቅ ድምፅ ነው የሚሰማኝ። የማስበው ሳየው ምን እንደምለው ነው! ሊመልስልኝ የሚችለውን መልስ መላ እመታለሁ። ልጅ እኔጋኮ ልጅ አለህ ስለው ይደነግጥ ይሆን? ይፀፀት ይሆን? እና? ቢለኝስ?

የሆነ ስም ጠርቶ እገሌ ይጠራልኝ ብሎ አባትየው ሲቀውጠው ፖሊሶቹ አልፈቅድ ብለው እንደሆነ ገባኝ። ከመምጣታችን በፊት አጣርቶ ነው ማለት ነው? ፍርሃቴ ከማየሉ የተነሳ እዚህ ድረስ ከመጣሁ በኋላ እንቢ ብለው ሳላገኘው ብመለስ ብዬ አስቤ ለቅፅበት ደስ እንደሚለኝ ተሰማኝ። ትልቁን ፍርሃቴን ተጋፍጬ ከእውነት ከመጋፈጥ መሸሽ!! የሰው ልጅ በብዙ እንደዛ አይደለ? ፍርሃቱን በመሸሽ ውስጥ ያለውን መንገድ ያውቀዋል። ቢወደውም ቢጠላውም ስለለመደው ይኖራል። ፍርሃቱን ሲጋፈጥ ከተራራው ጀርባ ያለውን ግን አያውቀውም። ሳያውቀው ይፈራዋል። አልለመደውማ! ስለዚህ ፍርሃቱን እሹሩሩ እያለ የለመደውን የተለመደ ህይወት ይኖራል።

የተባለው ሰው ተጠርቶ ተጨባብጠው። ሁኔታውን በእርጋታ ከተረዳዱ በኋላ ተስማሙ። ሰውየው አሸናፊ እንዲጠራ ትእዛዝ ሲሰጥ መሮጥ ሁሉ አማረኝ። ብቻ እነግሩም ስለተንቀሳቀሱ እግሬን ወደፊት እየዘረጋሁ ዘለቅኩ። ተጠርቶ ሲመጣ የሚቆምበት ቦታ የሆነ ፖሊስ ነገር እየመራ ወስዶ ሲያደርሰኝ እነ ግሩም ወደኋላ ቀሩ

ከጀርባው ለእኔ ከማይታየኝ ከሆነ ሰው ጋር እያወራ እየሳቀ ብቅ አለ። ሲያየኝ እንደመቆም አለ። ፊቱ ግን የገረመው አይመስልም ነበር። የሆነ ቀን እንደምመጣ የሚያውቅ ዓይነት መረጋጋት ነው ያለው። በረዥሙ ቢተነፍስ ትንፋሹ በሚሞቀኝ ዓይነት ርቀት ላይ ደርሶ ሲቆም ለምን ላገኘሁ እንደመጣሁ ፣ ምን ልጠይቀው እንደነበር ሀሳቤ ሁሉ ጭንቅላቴ ውስጥ ተደነባበረ። እልህ ፣እንባ ፣ላለመሸነፍ ትንቅንቅ ..... አፈነኝ። ወዲያው ደግሞ በራሴ ተበሳጨሁ። እንዴት ያለሁ ልፍስፍስ ነኝ ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንኳን የበደለኝን ሰው ሳየው ጎብዞ መታየት የሚከብደኝ? እኔ እስካወራ ድረስ ከንፈሩን አላላቀቀም። አይኖቹን እንኳን አልሰበራቸውም። ሳይነቅል ከማየቱ የተነሳ በአይኑ እየቦረቦረኝ ያለ ዓይነት ስሜት ሁላ ነው የተሰማኝ። ለደቂቃ ትንፋሼን ውጬ አይኖቼን አይኖቹ ውስጥ ዘፈዘፍኳቸው። አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር

"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው።

ይቀጥላል እንግዲህ......
236 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 መጥፎ ሴት አይደለሁም። ግን ደግሞ መልዓክም አይደለሁም። የአሸናፊን ልጅ ልንከባከብ? ራሴን ፈራሁት። እኔ እኮ በእርሱ ምክንያት ማንንም የማላምን ደንባራ ሴት ሆኛለሁ። ሙሽራዋ ከአንድ ዓመት በላይ አብሯት ለመዝለቅ ያልፈለጋት ምንም የሆነች ዓይነት ሴት እንደሆንኩ እየተሰማኝ ታምሜያለሁ። እኔኮ በእርሱ ምክንያት ፍቅርንም ሰው ማመንንም ሰው መቅረብንም አጠገቤ እንዳይደርሱ አርቄ ቀብሬያቸዋለሁ። የእርሱን ልጅ ላሳድግ? እናቱ አይበለውና ብትሞት እናቱ እሆናለሁ? ራሴን ፈራሁት ......

"እማዬስ?" አለኝ ባባ ሳሎን ገብቼ የደነዘዘ ሰውነቴን ሶፋው ላይ እንደጣልኩት። 'እናትህማ እኔን ፍም ላይ ማግዳኝ ሆስፒታል ተኝታለች' ብለው ደስ ባለኝ።

"ምነው እማ? ምን ሆንሽ?" አለችኝ ልጄ ተከትላ ..... እንደአዲስ ክው ብዬ ደነገጥኩ .... ምንድነው የምላት???

ምንም ከማለቴ በፊት ባባ

"እማዬጋ ውሰጂኝ!" ብሎ እሪታውን አቀለጠው።

ይቀጥላል። ...........
193 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #2

"የገጨሃት ቦታ ውሰደኝ ምናልባት ሰፈሯ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ስልኳን እዛ ጥላው ሊሆን ይችላል። የሚያውቃት ሰው ሊኖር ይችላል!"

በውስጤ ምናልባት ጎዳና ላይ ቢሆንስ የምትኖረው ብዬ አስቤያለሁ ጮክ ብዬ አላወራሁትም እንጂ ምናልባት ከነአካቴው ስልክም አልነበራት ይሆናል። መታወቂያዋ ላይ ያለውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ተከትዬ ቀበሌ ሄጄ ቤቷን ፍለጋ አስቤዋለሁ። ቀላል እንደማይሆን ግልፅ ነው። ቀበሌ አልወድም!!

"በፍፁም እኔ አልነዳም። ህም ...በጭራሽ መሪ አልይዝም። ታክሲ .....ራይድ ይጠራ" ሲል አሳዘነኝ ማንም ትኩረት ሰጥቶ እሱን ያየው የለም እንጂ እሱም ከባድ ድንጋጤ ላይ ነው። አሁንም እጆቹ እየተንቀጠቀጡ ነው። ሲያወራ መሸሻ ያጣ አይነት ዓይኖቹ መሬቱን ይምሳሉ። ይሄን እያለኝ ድርብብ ያሉ የሴት ወይዘሮ የሚያነክስ እግራቸውን በጌጠኛ ከዘራ እያገዙ የሚራመዱ ሰውዬ አስከትለው ወደ ክፍሉ ገቡ።

"ኪያዬ ......ደስ አላለኝም ! በለሊት አትጓዝ እያልኩህ ...." እያሉ እያገላበጡ ሲስሙት እና ደህና መሆኑን ሲያረጋግጡ ልጃቸው ተገጭቶ እንጂ እሱ ገጭቶ አይመስልም። እሱም እናቱን ሲያይ የሆነው የልጅ መሆን ካቀፍኩት ህፃን አይለይም ነበር። በኋላ እሱም ገብቶት ነው መሰለኝ ከእናቱ እቅፍ ወጥቶ በማፈር ሲያየኝ ነው ገና ሰው እንኳን መኖሩን እናትየው ያዩት።

"እባክሽ ልጄ አንድ ልጄ ነው በሽምግልና እንጨርሰው? (ባጌጠ ልብሳቸው እግሬ ስር ሲንበረከኩ ክብራቸው አላሳሰባቸውም። እናት ናቸዋ! ደንግጬ ደነዘዝኩ። ካሰብኩት በላይ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደተዘፈቅኩ ገባኝ። ከተንበረከኩበት ላነሳቸው እየሞከርኩ ከአፌ ግን ቃል አይወጣልኝም።) ካሱ የምንባለውን እንክሳለን። እናትየው እስኪሻላት ህፃኑንም ቢሆን ወስጄ እንከባከባለሁ። እባክሽ ልጄን አሳልፈሽ አትስጪብኝ?"

ለደቂቃ ህፃኑን ሰጥቻቸው ጭልጥ ብዬ መጥፋት ሁሉ አሰብኩ። ባባ ቀልቡ የነገረው ይመስል ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ። የተገጨችው እህቴ ብትሆን ምንድነበር የምወስነው? ብትሞት የእነሱ ካሳ የህይወት ካሳ ይሆናል? እሺ ጥፋቱ የሷስ ቢሆን? እንዳለው እሷ ብትሆንስ ዘው ብላ የገባችበት? ኸረ ምን አይነቷ ሴት ናት ግን እዚህ ጣጣ ውስጥ ዘፍቃኝ ማን እንደሆነች እንኳን የማላውቃት

"እባኮትን ይነሱ። እኔ ለራሴ ዞሮብኛል።"

የተፈጠረውን አስረዳኋቸው። አባትየው መታወቂያው ላይ ባለው አድራሻ ቤቱን ሊያፈላልጉ ሀላፊነት ወሰዱልኝ። ማን እንደሆነች እና ከእኔጋር የሚያዛምዳትን ነገር እስክደርስበት ባባ እኔጋ እንዲቆይ ወሰንኩ። እነርሱም የሚያስፈልገውን ሊያሟሉለት እና ሊጠይቁት ቃል ገቡልኝ። አንድ ላይ በእነርሱ መኪና እናትየው እየነዱ አደጋው የደረሰበት ቦታ ሄድን:: ምንም ነገር የለም። ከአልፎ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ውጪ በአካባቢው ማንም አይታይም። የመኖሪያ ሰፈርም አይደለም። ዓይኔ መሬቱ ላይ ካለ አንድ ብር ሳንቲም ላይ አረፈ። ደም ነክቶታል። ለምን እንዳነሳሁት አላውቅም ግን አነሳሁት። የሷ ይሆን? በእጇ ይዛው ነበር? ወድቆባት ልታነሳ ስትል ይሆን መኪናውን ያላየችው? ወይስ ሌላ ሰው የጣለው ሳንቲም ነው? ስልኬ ሲጠራ ባላወቅኩት ምክንያት ደንግጬ ዘለልኩ

"አይዞሽ አይዞሽ" አሉኝ እናትየው መደንበሬን ሲያዩ

"እማ በጠዋት የት ሄደሽ ነው? " ልጄ ናት። ቤቴን ረስቼዋለሁ። ሰዓቱን ረስቼዋለሁ። ዛሬ ቅዳሜ መሆኑንም እረስቼዋለሁ።

"መጣሁ እናቴ! ለባብሰሽ ጠብቂኝ" አልኳት ቅዳሜ ጠዋት ሁል ጊዜ እናትና አባቴ ጋር ነው ቁርስ የምንበላው።

እነርሱ ስልክ ተቀያይረን እቤት አድርሰውኝ ተመለሱ። የማልዋሸው በዛው ቢጠፉስ ብዬ አስቤያለሁ። ሰው ለማመን ቅርብ አይደለሁም። የመኪና ታርጋቸውን መዝግቤ መታወቂያቸውን ፎቶ ኮፒ አደረግኩ።

"እማ ትልቅ ሰው የሚበላውን ምግብ ይበላል ኸረ ጥርስኮ አለው" ትለኛለች ልጄ ለባባ ምግብ ምን ልስጠው ብዬ ስባዝን እየሳቀችብኝ። ልጄ 15 ዓመቷ ነው። በስንት ዓመቷ ምን እንደበላች ጠፍቶኛል። ለመጨረሻ ጊዜ ገላዋን መች እንዳጠብኳት ረስቼዋለሁ ..... ባባን አጣጥቤ እነእማዬጋ ተያይዘን ሄድን::

"እግዚአብሄር የሆነ ነገር ሊያስተምርሽ ነው ይሄን ህፃን ወደ ህይወትሽ ያመጣው" አለችኝ እናቴ የሆነውን ሁሉ ከነገርኳቸው በኋላ። ከቤተሰቡ አንድ ሰው እንኳን ድንገት ቢያውቃት ብዬ አስቤ ነበር:: ማንም አያውቃትም። (እናቴ ምን ማለቷ እንደሆነ አውቃለሁ። ማግባት አለብሽ ልጅ መድገም አለብሽ ነው ቅኔው። ወንድሜ በሚያስቀና ትዳር ሶስተኛ ልጁን ሰልሷል። የእኔ ያለባል መቅረት ያሳስባታል:: )

"እማ ደግሞ እግዚአብሄር እኔን ስለሚወደኝ እኔን ለማስተማር ይሄን ህፃን አይቀጣም! የሆነችን ሴት በመኪና አስገጭቶ ለኔ ትምህርት አይሰጥም። እነርሱምኮ ፍጡሮቹ ናቸው እኔን ለማስተማር ህይወታቸውን የሚያዘባርቅባቸው አሻንጉሊቶች አይደሉም!!" አልኳት። ወንድሜና አባቴ ተያይተው ጨዋታውን ቀየሩት። ከእማዬጋ እንዲህ አይነት ወሬ ከጀመርን ማባሪያ የሌለው ጭቅጭቅ እንደሆነ ያውቃሉ:: እዛው ቤተሰቦቼ ቤት ሆኜ ወደ ከሰዓት ስልኬ ጠራ ባባ ኩርምት ብሎ ከተኛ ሰዓታት አልፈውታል።

"አብርሃም ነኝ"

"አብረሃም? አብረሃም?"

"የግሩም አባት! ልጅቷን የገጫት ልጅ አባት... "
"እእ ....እሺ "

"የምትኖርበትን ቤት አግኝተነዋል። አከራዮችዋን አናግረን የእሷ ቤት መሆኑን አረጋግጠናል።"

"በዚህ ፍጥነት? እንዴት? ያውም በቅዳሜ?"

"ብዙም አስቸጋሪ አልነበረም:: የቤት ቁጥሩ የአከራዮችዋ ቤት ነው:: ደግሞስ የልጄ ጉዳይ አይደል? ይልቅ መምጣት ሳይኖርብሽ አይቀርም። ከባሏ ውጪ ማንም ዘመድም ሆነ የቅርብ ሰው እንደሌላት ነው የነገሩን።"

"ታዲያ ባሏ እያለ እኔን ምን ቤት ናት ብላ ነው የፃፈችኝ?"

"ባሏ ከታሰረ ሁለት ዓመት አልፎታል።"

"እሺ እኔ ምን ቤት ነኝ መታወቂያዋ ላይ የተገኘሁት? ወይ ፈጣሪ ! "

"እኔ ምን አውቄው ብለሽ? (እኔ አልፃፍኩሽ የሚል አንድምታ ባለው ለዛ) ምናልባት በባለቤትዋ? እስር ቤት ያለ የቅርብ ሰው ወይ ዘመድ የለሽም?"

"በፍፁም ኸረ እኔ ጭራሽ የታሰረ የሩቅም ሰው አላውቅም። "

"ምናልባት አከራዮችዋ ከሚነግሩሽ ነገር ፍንጭ ልታገኚ ስለምትችዪ ብትመጪ መልካም ይመስለኛል:: ብዙ አመት ኖራለች አብራቸው.... እ.... ባለቤቷ ... አሸናፊ ይባላል ነው ያሉኝ .......እንደው ካወቅሽው "

ከጀርባዬ የሆነ ነገር ማጅራቴን በሀይል የደለቀኝ ነገር መሰለኝ .........ጭው አለብኝ። አይሆንም። እሱማ አይሆንም! ሊሆን አይችልም።... ስም ተመሳስሎ ነው.... ማሰብ ተሳነኝ!!

"ምነው ሴትየዋ ሞተች እንዴ?" ትለኛለች የወንድሜ ሚስት ......

ይቀጥላላ ምን ታፐጣላችሁ???
184 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 አታምጣው ስለው .... አምጥቶ ቆለለው (ርዕስ ነው)

የስልኬ ጥሪ ነው ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ። ከንጋቱ 12:10

"ከሆስፒታል ነው የምንደውለው!! ዶክተር ፈቃደ እባላለሁ።"

"በየሱስም! እናቴ ምን ሆነች?" ብድግ ብዬ ቁጭ አልኩ:: ማታ ስኳሬ ከፍ ብሏል ስትለኝ ነበር።

"ወይዘሮ ሄለን አበራ አደጋ ገጥሟቸው ...."

"ሄለን አበራ? በስመአብ! (ልቤ ጉሮሮዬጋ ደርሳ ነበር ምልስ ብላ አቃፊዋ ውስጥ ስትገባ ታወቀኝ) ምነው እያጣራችሁ ብትደውሉ? በዚህ ጠዋት ያልታመምኩትን ሴትዮ በድንጋጤ ልትገሉኝ ነው እንዴ? ተሳስታችኋል!! እኔ ሄለን አበራ የምትባል ሴት አላውቅም! "

"ወይዘሮ ፌቨን አዳነ አይደሉም?"

"ነኝ!" አሁን ግራ ገባኝ። ስልኬን ቢሳሳት ስሜን ግን አስተካክሎ ሊጠራ አይችልም።

"የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ተብለው የተመዘገቡት እርሶ ኖት!" ከአልጋዬ በደመነፍስ ወረድኩ

"እህ እኔ እንዲህ የምትባል ሴት አላውቅማ? ቆይ የሆነውን አስረዳኝ ምን አይነት ሴት ናት? ምን አይነት አደጋ ነው የገጠማት?"

"የመኪና አደጋ ነው። ለጊዜው conscious አይደለችም:: ቦርሳዋ ውስጥ ባገኘነው መታወቂያ ላይ የእርሶን ስልክና ስም ነው ያገኘነው።"

"እሺ መጣሁ!" አልኩኝ ነገሩ ምንም ስሜት ሳይሰጠኝ ..... አደጋ ደርሶ ነው እየተባልኩ ከዛ በላይ ጥያቄ ማብዛት ክፋት ነገር መሰለኝ። የእኔን ስም የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ብሎ ሊመዘግብ የሚችል ዘመድ አሰብኩ ........ ምናልባት በቤት ስሟ የማውቃት ዘመድ ..... ጭንቅላቴ እዚህም እዛም እየረገጠ የተባልኩት ሆስፒታል ደረስኩ እና የተባለውን ዶክተር አገኘሁት። የተባለችው ሴት የተኛችበት ክፍል ወሰደኝ። ሰውነቷ በአብዛኛው በፋሻ ስለተጠቀለለ የማውቃት ሴት እንኳን ብትሆን መለየት አልችልም ነበር።

"የማውቃት አይመስለኝም!" አልኩት ግራ ገባቶኝ። ከጋውን ኪሱ መታወቂያዋን አውጥቶ ሰጠኝ። ሲገለባበጥ ሌላ ምስል ያሳየኝ ይመስል እያገለባበጥኩ አየሁት። በፍፁም አላውቃትም! ስሜና ስልክ ቁጥሬ ግን የመታወቂያው ጀርባ ላይ ቁልጭ ብሎ ተፅፏል። እድሜ 30 .... ቆንጅዬ ወጣት ናት። ፎቶዋ ላይ ጥርሷን ሳትገልጥ ፈገግ ብላለች። በወፋፍረሙ ተገምዶ ደረቷ ላይ የተዘናፈለ ፀጉር አላት ..... በፍፁም አይቻት አላውቅም።

"ማነው ሆስፒታል ያመጣት?" አልኩኝ ትክክለኛ ጥያቄ ይሁን ሳልረዳ

"አደጋ ያደረሰባት ሰው ነው ይዟት የመጣው። መጠበቂያ ክፍል ተቀምጧል ልታገኚው ከፈለግሽ? " ብሎ መልሴን ሳይጠብቅ በሩን ከፍቶ ወጣ ተከተልኩት የተባለው ሰው ከዶክተሩ ጋር ወደክፍሉ ስገባ ሲያየኝ ዘሎ ከመቀመጫው ተነሳ ..... አጠገቡ ተቀምጦ የነበረ በግምት የ4 ዓመት የሚሆን ህፃንም ተከትሎት ብድግ አለ።

"ቤተሰቧ ነሽ? ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላወቅኩም ነበር! እጄን ለፖሊስ ልስጥ? እሰጣለሁ በቃ! (መላ አካሉ ይንቀጠቀጣል።) ከየት መጣች ሳልላት ነው ዘው ብላ የገባችብኝ በቦታው የነበረ ሰውም አልነበረም። አልነጋምኮ .... የሞተች መስሎኝ ነበር !" ድንጋጤው እንዳለ ነው የለበሰው ጥቁር ሱፍና ነጭ ሸሚዝ በደም እንደተነከረ ነው። እጆቹ ላይ የቀረውን የደረቀ ደም ሊጠርገው ግድ ያለው አይመስልም ወይም ከነጭራሹ ደም እጁ ላይ መኖሩንም አላስተዋለውም። ግራ ገባኝ። ምንም በማላውቀው ክስተት ውስጥ የተነከርኩት እኔ ምን ልበል? አይኖቼ ህፃኑ ላይ መንቀዋለላቸውን ሲያይ

"ልጇ ነው። አብረው ነበሩ። እማ ብሎ ሲጮህ ነው ያየሁት እኔ እንጃ ምን እንደተፈጠረ። እሱ የእግረኛ መንገድ ላይ ነበረ። ቤተክርስቲያን እየሄዱ መሰለኝ ነጠላ ለብሳ ነበር። .... ቤተክርስትያን ለመሄድ ራሱ በቅጡ አልነጋም ነበር:: "

ምን እንደማደርግ ሳላውቅ ህፃኑጋ ተጠግቼ በርከክ አልኩ። ደነበረ። ትንንሽ እጆቹን ልይዛቸው እጄን ስዘረጋ ሰበሰባቸው።

"ስምህ ማነው?" አልኩት እናቱን መኪና ሲገጫት በአይኑ ካየ ሁለት ሰዓት ላልሞላው ህፃን የእኔ ጥያቄ ምኑ ነው? እኔስ ምኑ ነኝ? ዓለምስ ራሱ ምኑ ናት?

"ባባ" አለኝ የደረቁ ከንፈሮቹን እያላቀቀ

"ባባዬ እኔን ታውቀኛለህ?" አልኩት የማይጠየቅ ጥያቄ እንደሆነ እያወቅኩ። በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ።

"አባትህ የት እንደሆነ ታውቃለህ?" አሁንም በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ። ግራ ገባኝ! ይህቺ ሴት ማናት? ለምንስ ነው የማላውቃት ሴት መታወቂያ ላይ የእኔ ስም የሰፈፈረው?

"ዶክተር እሷ ያለችበትን ሁኔታ ንገረኝ? ትድናለች አይደል? " እንድከተለው ምልክት ሰጥቶኝ ወደ ቢሮ ይዞኝ ሄደ። ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደሆነ ለመገመት አልተቸገርኩም።

"ተጨማሪ ምርመራዎች አዝዣለሁ። ውጤቶቹ እስኪመጡ እርግጠኛ የሆነ ምላሽ ልሰጥሽ አልችልም። ጭንቅላቷ በሃይል ተጋጭቷል። እንዳልኩሽ ሁሉም ውጤት ሳይመጣ ብዙም ማለት አልችልም።"

"የምትድን ይመስልሃል ግን? የምትነቃ ይመስልሃል?"

"ይቅርታ ይሄን አሁን መናገር አልችልም።"

"እሺ እኔ ምን ላድርግ? አላውቃትምኮ? ህፃኑንስ ምን ላድርገው? ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት?"

"የማታውቂያት ከሆነ ሆስፒታሉ ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት" አለኝ። አላውቃትም ያልኩትን ግን ያመነኝ አይመስልም።

"እሺ የገጫትስ ሰውዬ?"

"ቤተሰብ ቢገኝ ወይ በሽምግልና ያልቃል ወይ ይከሱታል። እንደምትዪው የማታውቂያት ከሆነ ጉዳዩን ለፖሊስ ማሳወቅ ግዴታችን ነው። ሰውየው የማምለጥ ሀሳብ የለውም። ሲገጫት ማንም አላየውም ጥሎ መሄድ ይችል ነበር። ይልቅስ ያላነሰ ብር ከፍሎ የግል ሆስፒታል ሊያሳክማት ፈቃደኛ ከሆነ በህግ ይዳኝ በሽምግልና ቤተሰብ ነው የሚወስነው።"

ሁሉንም ጥዬ መሄድ ፈለግኩ። ምን አገባኝ እና ነው እዚህ ጣጣ ውስጥ የምገባው ብዬ ..... ወደመጠበቂያው ክፍል ስመለስ ህፃኑ የምስራች የምነግረው ይመስል ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ በተስፋ አይን አይኖቼን ሲያየኝ እግሬ የሚቀጥለውን እርምጃ መራመድ አቃተው:: አጠገቤ ደርሶ ትንሽዬ ፊቱን ወደ ላይ አንጋጦ እያየኝ ሊያለቅስ ጉንጩ እየተንቀጠቀጠ

"እማዬስ?" አለኝ:: እንባው ከፊደሎቹጋ ከአይኑ እየወረደ..... ከሱ ብሼ እንደህፃን ማልቀስ አማረኝ:: አቅፌ ብድግ እያደረግኩት በዛች ቅፅበት አብሬው እማገዳለሁ እንጂ እሳት ውስጥ ጥዬው እንደማልሄድ አወቅኩ። ...

ይቀጥላል ........

እንዴት ናችሁልኝ ግን እናንተ?
162 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 "እ? አዎ አይ እርግጠኛ ነኝ! ችግር የለውም!" አልኩኝ ደረቴን በርቅሳ ልትወጣ ይመስል የምትደልቅ ልቤን እንዳያዩብኝ ልብሴን እየነካካሁ። ምንም ባልናገርም ፊቱን ማየት እንደሞት እንዳስፈራኝ ከሁኔታዬ ገብቷቸዋል።

አባትየው ለአንደኛው ፖሊስ ሲያስረዳ ሲጨቃጨቁ አጠገባቸው ሆኜ እንደእሩቅ ድምፅ ነው የሚሰማኝ። የማስበው ሳየው ምን እንደምለው ነው! ሊመልስልኝ የሚችለውን መልስ መላ እመታለሁ። ልጅ እኔጋኮ ልጅ አለህ ስለው ይደነግጥ ይሆን? ይፀፀት ይሆን? እና? ቢለኝስ?

የሆነ ስም ጠርቶ እገሌ ይጠራልኝ ብሎ አባትየው ሲቀውጠው ፖሊሶቹ አልፈቅድ ብለው እንደሆነ ገባኝ። ከመምጣታችን በፊት አጣርቶ ነው ማለት ነው? ፍርሃቴ ከማየሉ የተነሳ እዚህ ድረስ ከመጣሁ በኋላ እንቢ ብለው ሳላገኘው ብመለስ ብዬ አስቤ ለቅፅበት ደስ እንደሚለኝ ተሰማኝ። ትልቁን ፍርሃቴን ተጋፍጬ ከእውነት ከመጋፈጥ መሸሽ!! የሰው ልጅ በብዙ እንደዛ አይደለ? ፍርሃቱን በመሸሽ ውስጥ ያለውን መንገድ ያውቀዋል። ቢወደውም ቢጠላውም ስለለመደው ይኖራል። ፍርሃቱን ሲጋፈጥ ከተራራው ጀርባ ያለውን ግን አያውቀውም። ሳያውቀው ይፈራዋል። አልለመደውማ! ስለዚህ ፍርሃቱን እሹሩሩ እያለ የለመደውን የተለመደ ህይወት ይኖራል።

የተባለው ሰው ተጠርቶ ተጨባብጠው። ሁኔታውን በእርጋታ ከተረዳዱ በኋላ ተስማሙ። ሰውየው አሸናፊ እንዲጠራ ትእዛዝ ሲሰጥ መሮጥ ሁሉ አማረኝ። ብቻ እነግሩም ስለተንቀሳቀሱ እግሬን ወደፊት እየዘረጋሁ ዘለቅኩ። ተጠርቶ ሲመጣ የሚቆምበት ቦታ የሆነ ፖሊስ ነገር እየመራ ወስዶ ሲያደርሰኝ እነ ግሩም ወደኋላ ቀሩ

ከጀርባው ለእኔ ከማይታየኝ ከሆነ ሰው ጋር እያወራ እየሳቀ ብቅ አለ። ሲያየኝ እንደመቆም አለ። ፊቱ ግን የገረመው አይመስልም ነበር። የሆነ ቀን እንደምመጣ የሚያውቅ ዓይነት መረጋጋት ነው ያለው። በረዥሙ ቢተነፍስ ትንፋሹ በሚሞቀኝ ዓይነት ርቀት ላይ ደርሶ ሲቆም ለምን ላገኘሁ እንደመጣሁ ፣ ምን ልጠይቀው እንደነበር ሀሳቤ ሁሉ ጭንቅላቴ ውስጥ ተደነባበረ። እልህ ፣እንባ ፣ላለመሸነፍ ትንቅንቅ ..... አፈነኝ። ወዲያው ደግሞ በራሴ ተበሳጨሁ። እንዴት ያለሁ ልፍስፍስ ነኝ ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንኳን የበደለኝን ሰው ሳየው ጎብዞ መታየት የሚከብደኝ? እኔ እስካወራ ድረስ ከንፈሩን አላላቀቀም። አይኖቹን እንኳን አልሰበራቸውም። ሳይነቅል ከማየቱ የተነሳ በአይኑ እየቦረቦረኝ ያለ ዓይነት ስሜት ሁላ ነው የተሰማኝ። ለደቂቃ ትንፋሼን ውጬ አይኖቼን አይኖቹ ውስጥ ዘፈዘፍኳቸው። አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር

"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው።

ይቀጥላል እንግዲህ......
146 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #2

"የገጨሃት ቦታ ውሰደኝ ምናልባት ሰፈሯ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ስልኳን እዛ ጥላው ሊሆን ይችላል። የሚያውቃት ሰው ሊኖር ይችላል!"

በውስጤ ምናልባት ጎዳና ላይ ቢሆንስ የምትኖረው ብዬ አስቤያለሁ ጮክ ብዬ አላወራሁትም እንጂ ምናልባት ከነአካቴው ስልክም አልነበራት ይሆናል። መታወቂያዋ ላይ ያለውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ተከትዬ ቀበሌ ሄጄ ቤቷን ፍለጋ አስቤዋለሁ። ቀላል እንደማይሆን ግልፅ ነው። ቀበሌ አልወድም!!

"በፍፁም እኔ አልነዳም። ህም ...በጭራሽ መሪ አልይዝም። ታክሲ .....ራይድ ይጠራ" ሲል አሳዘነኝ ማንም ትኩረት ሰጥቶ እሱን ያየው የለም እንጂ እሱም ከባድ ድንጋጤ ላይ ነው። አሁንም እጆቹ እየተንቀጠቀጡ ነው። ሲያወራ መሸሻ ያጣ አይነት ዓይኖቹ መሬቱን ይምሳሉ። ይሄን እያለኝ ድርብብ ያሉ የሴት ወይዘሮ የሚያነክስ እግራቸውን በጌጠኛ ከዘራ እያገዙ የሚራመዱ ሰውዬ አስከትለው ወደ ክፍሉ ገቡ።

"ኪያዬ ......ደስ አላለኝም ! በለሊት አትጓዝ እያልኩህ ...." እያሉ እያገላበጡ ሲስሙት እና ደህና መሆኑን ሲያረጋግጡ ልጃቸው ተገጭቶ እንጂ እሱ ገጭቶ አይመስልም። እሱም እናቱን ሲያይ የሆነው የልጅ መሆን ካቀፍኩት ህፃን አይለይም ነበር። በኋላ እሱም ገብቶት ነው መሰለኝ ከእናቱ እቅፍ ወጥቶ በማፈር ሲያየኝ ነው ገና ሰው እንኳን መኖሩን እናትየው ያዩት።

"እባክሽ ልጄ አንድ ልጄ ነው በሽምግልና እንጨርሰው? (ባጌጠ ልብሳቸው እግሬ ስር ሲንበረከኩ ክብራቸው አላሳሰባቸውም። እናት ናቸዋ! ደንግጬ ደነዘዝኩ። ካሰብኩት በላይ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደተዘፈቅኩ ገባኝ። ከተንበረከኩበት ላነሳቸው እየሞከርኩ ከአፌ ግን ቃል አይወጣልኝም።) ካሱ የምንባለውን እንክሳለን። እናትየው እስኪሻላት ህፃኑንም ቢሆን ወስጄ እንከባከባለሁ። እባክሽ ልጄን አሳልፈሽ አትስጪብኝ?"

ለደቂቃ ህፃኑን ሰጥቻቸው ጭልጥ ብዬ መጥፋት ሁሉ አሰብኩ። ባባ ቀልቡ የነገረው ይመስል ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ። የተገጨችው እህቴ ብትሆን ምንድነበር የምወስነው? ብትሞት የእነሱ ካሳ የህይወት ካሳ ይሆናል? እሺ ጥፋቱ የሷስ ቢሆን? እንዳለው እሷ ብትሆንስ ዘው ብላ የገባችበት? ኸረ ምን አይነቷ ሴት ናት ግን እዚህ ጣጣ ውስጥ ዘፍቃኝ ማን እንደሆነች እንኳን የማላውቃት

"እባኮትን ይነሱ። እኔ ለራሴ ዞሮብኛል።"

የተፈጠረውን አስረዳኋቸው። አባትየው መታወቂያው ላይ ባለው አድራሻ ቤቱን ሊያፈላልጉ ሀላፊነት ወሰዱልኝ። ማን እንደሆነች እና ከእኔጋር የሚያዛምዳትን ነገር እስክደርስበት ባባ እኔጋ እንዲቆይ ወሰንኩ። እነርሱም የሚያስፈልገውን ሊያሟሉለት እና ሊጠይቁት ቃል ገቡልኝ። አንድ ላይ በእነርሱ መኪና እናትየው እየነዱ አደጋው የደረሰበት ቦታ ሄድን:: ምንም ነገር የለም። ከአልፎ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ውጪ በአካባቢው ማንም አይታይም። የመኖሪያ ሰፈርም አይደለም። ዓይኔ መሬቱ ላይ ካለ አንድ ብር ሳንቲም ላይ አረፈ። ደም ነክቶታል። ለምን እንዳነሳሁት አላውቅም ግን አነሳሁት። የሷ ይሆን? በእጇ ይዛው ነበር? ወድቆባት ልታነሳ ስትል ይሆን መኪናውን ያላየችው? ወይስ ሌላ ሰው የጣለው ሳንቲም ነው? ስልኬ ሲጠራ ባላወቅኩት ምክንያት ደንግጬ ዘለልኩ

"አይዞሽ አይዞሽ" አሉኝ እናትየው መደንበሬን ሲያዩ

"እማ በጠዋት የት ሄደሽ ነው? " ልጄ ናት። ቤቴን ረስቼዋለሁ። ሰዓቱን ረስቼዋለሁ። ዛሬ ቅዳሜ መሆኑንም እረስቼዋለሁ።

"መጣሁ እናቴ! ለባብሰሽ ጠብቂኝ" አልኳት ቅዳሜ ጠዋት ሁል ጊዜ እናትና አባቴ ጋር ነው ቁርስ የምንበላው።

እነርሱ ስልክ ተቀያይረን እቤት አድርሰውኝ ተመለሱ። የማልዋሸው በዛው ቢጠፉስ ብዬ አስቤያለሁ። ሰው ለማመን ቅርብ አይደለሁም። የመኪና ታርጋቸውን መዝግቤ መታወቂያቸውን ፎቶ ኮፒ አደረግኩ።

"እማ ትልቅ ሰው የሚበላውን ምግብ ይበላል ኸረ ጥርስኮ አለው" ትለኛለች ልጄ ለባባ ምግብ ምን ልስጠው ብዬ ስባዝን እየሳቀችብኝ። ልጄ 15 ዓመቷ ነው። በስንት ዓመቷ ምን እንደበላች ጠፍቶኛል። ለመጨረሻ ጊዜ ገላዋን መች እንዳጠብኳት ረስቼዋለሁ ..... ባባን አጣጥቤ እነእማዬጋ ተያይዘን ሄድን::

"እግዚአብሄር የሆነ ነገር ሊያስተምርሽ ነው ይሄን ህፃን ወደ ህይወትሽ ያመጣው" አለችኝ እናቴ የሆነውን ሁሉ ከነገርኳቸው በኋላ። ከቤተሰቡ አንድ ሰው እንኳን ድንገት ቢያውቃት ብዬ አስቤ ነበር:: ማንም አያውቃትም። (እናቴ ምን ማለቷ እንደሆነ አውቃለሁ። ማግባት አለብሽ ልጅ መድገም አለብሽ ነው ቅኔው። ወንድሜ በሚያስቀና ትዳር ሶስተኛ ልጁን ሰልሷል። የእኔ ያለባል መቅረት ያሳስባታል:: )

"እማ ደግሞ እግዚአብሄር እኔን ስለሚወደኝ እኔን ለማስተማር ይሄን ህፃን አይቀጣም! የሆነችን ሴት በመኪና አስገጭቶ ለኔ ትምህርት አይሰጥም። እነርሱምኮ ፍጡሮቹ ናቸው እኔን ለማስተማር ህይወታቸውን የሚያዘባርቅባቸው አሻንጉሊቶች አይደሉም!!" አልኳት። ወንድሜና አባቴ ተያይተው ጨዋታውን ቀየሩት። ከእማዬጋ እንዲህ አይነት ወሬ ከጀመርን ማባሪያ የሌለው ጭቅጭቅ እንደሆነ ያውቃሉ:: እዛው ቤተሰቦቼ ቤት ሆኜ ወደ ከሰዓት ስልኬ ጠራ ባባ ኩርምት ብሎ ከተኛ ሰዓታት አልፈውታል።

"አብርሃም ነኝ"

"አብረሃም? አብረሃም?"

"የግሩም አባት! ልጅቷን የገጫት ልጅ አባት... "
"እእ ....እሺ "

"የምትኖርበትን ቤት አግኝተነዋል። አከራዮችዋን አናግረን የእሷ ቤት መሆኑን አረጋግጠናል።"

"በዚህ ፍጥነት? እንዴት? ያውም በቅዳሜ?"

"ብዙም አስቸጋሪ አልነበረም:: የቤት ቁጥሩ የአከራዮችዋ ቤት ነው:: ደግሞስ የልጄ ጉዳይ አይደል? ይልቅ መምጣት ሳይኖርብሽ አይቀርም። ከባሏ ውጪ ማንም ዘመድም ሆነ የቅርብ ሰው እንደሌላት ነው የነገሩን።"

"ታዲያ ባሏ እያለ እኔን ምን ቤት ናት ብላ ነው የፃፈችኝ?"

"ባሏ ከታሰረ ሁለት ዓመት አልፎታል።"

"እሺ እኔ ምን ቤት ነኝ መታወቂያዋ ላይ የተገኘሁት? ወይ ፈጣሪ ! "

"እኔ ምን አውቄው ብለሽ? (እኔ አልፃፍኩሽ የሚል አንድምታ ባለው ለዛ) ምናልባት በባለቤትዋ? እስር ቤት ያለ የቅርብ ሰው ወይ ዘመድ የለሽም?"

"በፍፁም ኸረ እኔ ጭራሽ የታሰረ የሩቅም ሰው አላውቅም። "

"ምናልባት አከራዮችዋ ከሚነግሩሽ ነገር ፍንጭ ልታገኚ ስለምትችዪ ብትመጪ መልካም ይመስለኛል:: ብዙ አመት ኖራለች አብራቸው.... እ.... ባለቤቷ ... አሸናፊ ይባላል ነው ያሉኝ .......እንደው ካወቅሽው "

ከጀርባዬ የሆነ ነገር ማጅራቴን በሀይል የደለቀኝ ነገር መሰለኝ .........ጭው አለብኝ። አይሆንም። እሱማ አይሆንም! ሊሆን አይችልም።... ስም ተመሳስሎ ነው.... ማሰብ ተሳነኝ!!

"ምነው ሴትየዋ ሞተች እንዴ?" ትለኛለች የወንድሜ ሚስት ......

ይቀጥላላ ምን ታፐጣላችሁ???
147 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:08:47 አታምጣው ስለው .... አምጥቶ ቆለለው #1(ርዕስ ነው)

የስልኬ ጥሪ ነው ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ። ከንጋቱ 12:10

"ከሆስፒታል ነው የምንደውለው!! ዶክተር ፈቃደ እባላለሁ።"

"በየሱስም! እናቴ ምን ሆነች?" ብድግ ብዬ ቁጭ አልኩ:: ማታ ስኳሬ ከፍ ብሏል ስትለኝ ነበር።

"ወይዘሮ ሄለን አበራ አደጋ ገጥሟቸው ...."

"ሄለን አበራ? በስመአብ! (ልቤ ጉሮሮዬጋ ደርሳ ነበር ምልስ ብላ አቃፊዋ ውስጥ ስትገባ ታወቀኝ) ምነው እያጣራችሁ ብትደውሉ? በዚህ ጠዋት ያልታመምኩትን ሴትዮ በድንጋጤ ልትገሉኝ ነው እንዴ? ተሳስታችኋል!! እኔ ሄለን አበራ የምትባል ሴት አላውቅም! "

"ወይዘሮ ፌቨን አዳነ አይደሉም?"

"ነኝ!" አሁን ግራ ገባኝ። ስልኬን ቢሳሳት ስሜን ግን አስተካክሎ ሊጠራ አይችልም።

"የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ተብለው የተመዘገቡት እርሶ ኖት!" ከአልጋዬ በደመነፍስ ወረድኩ

"እህ እኔ እንዲህ የምትባል ሴት አላውቅማ? ቆይ የሆነውን አስረዳኝ ምን አይነት ሴት ናት? ምን አይነት አደጋ ነው የገጠማት?"

"የመኪና አደጋ ነው። ለጊዜው conscious አይደለችም:: ቦርሳዋ ውስጥ ባገኘነው መታወቂያ ላይ የእርሶን ስልክና ስም ነው ያገኘነው።"

"እሺ መጣሁ!" አልኩኝ ነገሩ ምንም ስሜት ሳይሰጠኝ ..... አደጋ ደርሶ ነው እየተባልኩ ከዛ በላይ ጥያቄ ማብዛት ክፋት ነገር መሰለኝ። የእኔን ስም የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ብሎ ሊመዘግብ የሚችል ዘመድ አሰብኩ ........ ምናልባት በቤት ስሟ የማውቃት ዘመድ ..... ጭንቅላቴ እዚህም እዛም እየረገጠ የተባልኩት ሆስፒታል ደረስኩ እና የተባለውን ዶክተር አገኘሁት። የተባለችው ሴት የተኛችበት ክፍል ወሰደኝ። ሰውነቷ በአብዛኛው በፋሻ ስለተጠቀለለ የማውቃት ሴት እንኳን ብትሆን መለየት አልችልም ነበር።

"የማውቃት አይመስለኝም!" አልኩት ግራ ገባቶኝ። ከጋውን ኪሱ መታወቂያዋን አውጥቶ ሰጠኝ። ሲገለባበጥ ሌላ ምስል ያሳየኝ ይመስል እያገለባበጥኩ አየሁት። በፍፁም አላውቃትም! ስሜና ስልክ ቁጥሬ ግን የመታወቂያው ጀርባ ላይ ቁልጭ ብሎ ተፅፏል። እድሜ 30 .... ቆንጅዬ ወጣት ናት። ፎቶዋ ላይ ጥርሷን ሳትገልጥ ፈገግ ብላለች። በወፋፍረሙ ተገምዶ ደረቷ ላይ የተዘናፈለ ፀጉር አላት ..... በፍፁም አይቻት አላውቅም።

"ማነው ሆስፒታል ያመጣት?" አልኩኝ ትክክለኛ ጥያቄ ይሁን ሳልረዳ

"አደጋ ያደረሰባት ሰው ነው ይዟት የመጣው። መጠበቂያ ክፍል ተቀምጧል ልታገኚው ከፈለግሽ? " ብሎ መልሴን ሳይጠብቅ በሩን ከፍቶ ወጣ ተከተልኩት የተባለው ሰው ከዶክተሩ ጋር ወደክፍሉ ስገባ ሲያየኝ ዘሎ ከመቀመጫው ተነሳ ..... አጠገቡ ተቀምጦ የነበረ በግምት የ4 ዓመት የሚሆን ህፃንም ተከትሎት ብድግ አለ።

"ቤተሰቧ ነሽ? ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላወቅኩም ነበር! እጄን ለፖሊስ ልስጥ? እሰጣለሁ በቃ! (መላ አካሉ ይንቀጠቀጣል።) ከየት መጣች ሳልላት ነው ዘው ብላ የገባችብኝ በቦታው የነበረ ሰውም አልነበረም። አልነጋምኮ .... የሞተች መስሎኝ ነበር !" ድንጋጤው እንዳለ ነው የለበሰው ጥቁር ሱፍና ነጭ ሸሚዝ በደም እንደተነከረ ነው። እጆቹ ላይ የቀረውን የደረቀ ደም ሊጠርገው ግድ ያለው አይመስልም ወይም ከነጭራሹ ደም እጁ ላይ መኖሩንም አላስተዋለውም። ግራ ገባኝ። ምንም በማላውቀው ክስተት ውስጥ የተነከርኩት እኔ ምን ልበል? አይኖቼ ህፃኑ ላይ መንቀዋለላቸውን ሲያይ

"ልጇ ነው። አብረው ነበሩ። እማ ብሎ ሲጮህ ነው ያየሁት እኔ እንጃ ምን እንደተፈጠረ። እሱ የእግረኛ መንገድ ላይ ነበረ። ቤተክርስቲያን እየሄዱ መሰለኝ ነጠላ ለብሳ ነበር። .... ቤተክርስትያን ለመሄድ ራሱ በቅጡ አልነጋም ነበር:: "

ምን እንደማደርግ ሳላውቅ ህፃኑጋ ተጠግቼ በርከክ አልኩ። ደነበረ። ትንንሽ እጆቹን ልይዛቸው እጄን ስዘረጋ ሰበሰባቸው።

"ስምህ ማነው?" አልኩት እናቱን መኪና ሲገጫት በአይኑ ካየ ሁለት ሰዓት ላልሞላው ህፃን የእኔ ጥያቄ ምኑ ነው? እኔስ ምኑ ነኝ? ዓለምስ ራሱ ምኑ ናት?

"ባባ" አለኝ የደረቁ ከንፈሮቹን እያላቀቀ

"ባባዬ እኔን ታውቀኛለህ?" አልኩት የማይጠየቅ ጥያቄ እንደሆነ እያወቅኩ። በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ።

"አባትህ የት እንደሆነ ታውቃለህ?" አሁንም በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ። ግራ ገባኝ! ይህቺ ሴት ማናት? ለምንስ ነው የማላውቃት ሴት መታወቂያ ላይ የእኔ ስም የሰፈፈረው?

"ዶክተር እሷ ያለችበትን ሁኔታ ንገረኝ? ትድናለች አይደል? " እንድከተለው ምልክት ሰጥቶኝ ወደ ቢሮ ይዞኝ ሄደ። ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደሆነ ለመገመት አልተቸገርኩም።

"ተጨማሪ ምርመራዎች አዝዣለሁ። ውጤቶቹ እስኪመጡ እርግጠኛ የሆነ ምላሽ ልሰጥሽ አልችልም። ጭንቅላቷ በሃይል ተጋጭቷል። እንዳልኩሽ ሁሉም ውጤት ሳይመጣ ብዙም ማለት አልችልም።"

"የምትድን ይመስልሃል ግን? የምትነቃ ይመስልሃል?"

"ይቅርታ ይሄን አሁን መናገር አልችልም።"

"እሺ እኔ ምን ላድርግ? አላውቃትምኮ? ህፃኑንስ ምን ላድርገው? ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት?"

"የማታውቂያት ከሆነ ሆስፒታሉ ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት" አለኝ። አላውቃትም ያልኩትን ግን ያመነኝ አይመስልም።

"እሺ የገጫትስ ሰውዬ?"

"ቤተሰብ ቢገኝ ወይ በሽምግልና ያልቃል ወይ ይከሱታል። እንደምትዪው የማታውቂያት ከሆነ ጉዳዩን ለፖሊስ ማሳወቅ ግዴታችን ነው። ሰውየው የማምለጥ ሀሳብ የለውም። ሲገጫት ማንም አላየውም ጥሎ መሄድ ይችል ነበር። ይልቅስ ያላነሰ ብር ከፍሎ የግል ሆስፒታል ሊያሳክማት ፈቃደኛ ከሆነ በህግ ይዳኝ በሽምግልና ቤተሰብ ነው የሚወስነው።"

ሁሉንም ጥዬ መሄድ ፈለግኩ። ምን አገባኝ እና ነው እዚህ ጣጣ ውስጥ የምገባው ብዬ ..... ወደመጠበቂያው ክፍል ስመለስ ህፃኑ የምስራች የምነግረው ይመስል ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ በተስፋ አይን አይኖቼን ሲያየኝ እግሬ የሚቀጥለውን እርምጃ መራመድ አቃተው:: አጠገቤ ደርሶ ትንሽዬ ፊቱን ወደ ላይ አንጋጦ እያየኝ ሊያለቅስ ጉንጩ እየተንቀጠቀጠ

"እማዬስ?" አለኝ:: እንባው ከፊደሎቹጋ ከአይኑ እየወረደ..... ከሱ ብሼ እንደህፃን ማልቀስ አማረኝ:: አቅፌ ብድግ እያደረግኩት በዛች ቅፅበት አብሬው እማገዳለሁ እንጂ እሳት ውስጥ ጥዬው እንደማልሄድ አወቅኩ። ...

ይቀጥላል ........

እንዴት ናችሁልኝ ግን እናንተ?
149 views @du , 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 22:02:51 ነፍስ ይማር

ስለ'ኔ ስላንቺ
ካህናት በወረብ ፣ ሼሆች በመንዙማ
ባርምሞም በጩኸት፤
ይቀኛሉ ቅኔ ፣ ይዜማሉ ዜማ
ቅዱስ ለፍቅራችን
ቅዱስ ለጠባችን
ቅዱስ ለፍጻሜው
በ'ንባሽ ታንቆ ፍቅር ፣ ላለቀበት እድሜው
ስብሃት ሶስቴ ላንቺ ፣ ስብሃት ደግሞ ለ'ኔ
ለደከመው አካል ፣ ለደቀቀው ጎኔ
ፍትሃት ለዛ ፍቅር ፣ ፍትሃት ለዛ ተስፋ
በኩርፊያሽ ተዳፍኖ ፣ በእምባሽ ለጠፋ
ወዩ ለትግስትሽ ፣ ሞቷል መጠበቄ
ነፍስ ይማር ለሳቅሽ ፣ ነፍስ ይማር ለሳቄ

[ቶማስ ትግስቱ]
253 views @du , 19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ