አንዴ ጓደኛዬ ራሴን አጠፋለሁ ብሎ ተነሳ፡፡ ሁሉም ይመክረው ጀመር፡፡ ግን እሱ አሻፈረኝ አለ - ራሴን አጠፋለሁ አለ፡፡
ቤተሰቦቹ ጨነቃቸው፡፡ አባቱ እየሮጡ መጡና፣ “ይሄን ልጅ አልቻልነውም፤ ከእኛ አቅም በላይ ሆኗል…” አሉኝ፡፡ አባቱ አይወዱኝም ነበር አሁን ግን “ያለው ብቸኛ አማራጭ ይሄ ነው” ብለው አስበዋል…“ችግር የለውም እመጣለሁ” አልኳቸው፡፡ ቤታቸው ሄጄ ነገሩን ከሰማሁ በኋላ “ይሄውልህ…” አልኩት፣ “ሐሳብህ በጣም ጥሩ ነው፡፡ ትክክል ነው ብዬ አላስብም፡፡ ቢሆንም ግን ራሴን አጠፋለሁ ብለህ ከተነሳህ መቼስ ምን
ማድረግ እችላለሁ፡፡ ጓደኛዬ ስለሆንክ ረዳሃለሁ፡፡ ራሴን ካላጠፋሁ ካልክ - ጥሩ!! ውሳኔህ ትክክል አይመስለኝም ምክንያቱም እኔ ባንተ ቦታ ብሆን ጨርሶ ራሴን አላጠፋም ነበር፡፡ ምክንያቱም ሞኝነት ነዋ፡፡
አንዲት
ሴት እምቢ ስላለችህ ራስህን ታጠፋለህ? በሚሊየን የሚቆጠሩ
ሴቶች እያሉ አንዲት ሴት እምቢ አለችኝ ብለህ ራስህን ማጥፋት ተገቢ ውሳኔ አይደለም፡፡ በወር ውስጥ ረስተሃት ሌላ ማፍቀርህ አይቀርም ነበር፡፡ ግን ራሴን አጠፋለሁ ካልክ ምን ማድረግ ይቻላል …ጥሩ!! የራስህ ሕይወት የራስህ ነው…” አባትዬው ይህን ሲሰሙ በጣም ተረበሹ፡፡ “ጭራሽ ራስህን አጥፋ ትለዋለዋህ እንዴ… እኛ እኮ ያመጣንህ ይሄን ሐሳቡን ታስተወዋለህ ብለን ነው” አሉ አባትዬው፡፡ “እኛ ምን ስለሆንን ነው የምንረዳው?እርስዎ ሲወልዱት ጠይቀውታል እንዴ… ወደዚህች ምድር መምጣት ትፈልጋለህ ወይ ብለው ጠይቀውት ነበር? እና አሁን ለምንድነው ራሴን ላጥፋ ሲል የምትከለክሉት? ራሴን ላጥፋ ካለ ፍቀዱለት” ወደ ቤቴ ይዤው ሄድኩ…“ና እንሂድ… ራስህን ልታጠፋ አይደለ እስኪ እስከዛው ዘና እንበል እንዝናና፡፡ እስቲ አንድ ለሊት አብረን አናሳልፍ፡፡ እኔጋ እደር፡፡ ምናልባት የሆነ ቦታ እንገናኝ ይሆናል ምናልባትም ከዚህ በኋላ መቼም ላንገናኝ እንችላለን” አልኩት፡፡ እኔ ቤት ሆነን ቀስ በቀስ ማሰብ ጀመረ፡፡ ምክንያቱም እኔ በምንም መልኩ ሀሳቡን ለማስቀየር አልፈለግኩም፡፡ “አሁን የሚጮህ ሰዓት እንሙላና እንተኛ…” አልኩት፣ “ሌሊት 10 ሰዓት ሲሆን ተነስተን አንድ የሚያምር ቦታ እወስድሃለሁ፡፡ በጣም የሚያምር ቦታ ነው፡፡ ከዚያ ቦታ ላይ በቀላሉ ዘልለህ ወንዙ ውስጥ መፈጥፈጥ ትችላለህ። ከእኔም ጋር እዛው እንሰነባበታለን” ልክ 10 ሰዓት ላይ ሰዓቱ ሲጮህ ከአልጋው ጎትቼ ሳስነሳው፣ “አንተ ቆይ ምን አረግኩህ…” አለ ጮሆ፤ “ጠላቴ ነህ ወይስ ምንድነው? በቃ ራሴን ማጥፋት አልፈልግም!! “ይሄማ ትክክል አይደለም… አንዴ ወስነህ የለ እንዴ… የምን መወላወል ነው” “እንዴ በቃ ራሴን አላጠፋም!!እንድሞት ፈልገህ ነው። አልሞትም… በቃ… አልፈልግም ራሴን አላጠፋም… ሕይወቴን እወዳታለሁ” “እምቢ ካልክ አላስገድድህም” አልኩት…
እናም ራሱን አላጠፋም!!! አሁን አግብቶ ልጆች ወልዷል፡፡ መንገድ ላይ ካየኝ መንገድ አሳብሮ ነው የሚጠፋው፡፡ “አሁን ምን ተገኘና ነው” እለዋለሁ መንገድ ላይ ሳገኘው፣
“መቼም አላፈቅርም ብለኸኝ አልነበረም እንዴ… እንደገና አፍቅረህ አረፍከው!!!” እሱም እንዲህ ይለኛል፣ “በዕውነቱ እንኳንም ያቺ ልጅ እምቢ አለችኝ፡፡ ለእኔ አትሆነኝም ነበር ታሳብደኝ ነበር፡፡ እኔ አሁን የተሻለች ልጅ ነው ያገባሁት ።
(ኦሾ)
╔═══❖• •❖═══╗
@yefkrinegri
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@yenhiwet