Get Mystery Box with random crypto!

Hubil resul

የቴሌግራም ቻናል አርማ yarebi_aman — Hubil resul H
የቴሌግራም ቻናል አርማ yarebi_aman — Hubil resul
የሰርጥ አድራሻ: @yarebi_aman
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 101
የሰርጥ መግለጫ

ለናንተ ይሆናል ብለን ያሰብነዉን ኢስላማዊ ትምህርቶችን ይዘን እናቀርባለን
እና ያልተመቻቹን ነገር ንገሩን
ለአላህ ብለን እንወዳቹሀለን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-22 11:32:29
84 views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 10:28:36
ኧረ! ልቦለድ ቅጥፈት! ለካ እንዲህ ነው ዝም ብሎ የሚያቄሏቸው!


ኧረ! በአላህ




ምን አይነት ዐረብኛ ነው የሚያወራው?

ወላሂ! በቃ! ተከታዮቻቸውን እንደ በግ ነው የሚያይዋቸው ማለት ነው።

ምን ያክል ቢንቃቸው ነው እንዲህ የሚያደርገው?

ምንድን ነው ያለው ግን¿


ሸሃውዚን ሸሃውዚን ነፋሃይነ ነፋይነ…


በሳቅ¡
ስለ ሐፈዘው እስኪ ያለውን ይድገመው¿


ደግሞ ይሄንኑ "ዐረብኛውን" ሲያነበው አፈጣጠኑ¡
59 views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 09:57:57
# ስታሳዝን
ይህች አንጀት የምትበላ ህፃን # ኢልሀም_ንጉስ ትባላለች!የ7ተኛ ክፍል ጎበዝ
ተማሪ ነበረች!ድንገት
መድከምና ማዞር ሲጀምራት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለምርመራ ትሄዳለች!!
በሚያሳዝን ሁኔታ የ13ዓመቷ # ኢልሀም የአጥንት መቅኔዋ ደም ማምረት
እንዳቆመና በአስቸኳይ ወደ
ውጪ ሄዳ መታከም እንዳለባት ይነገራታል
# ለ3ወራትም ያለማቆረጥ በማህፀኗ ደም ፈሷታል
አባት ትቷት ሄዶ እናትም ለአመታት በስደት አጎንብሳ ብቻዋን እየተሰቃየች
አሳድጋት ደረሰችልኝ ስትል
# ሞት ቀድሞ ልጇን ሊነጥቅባት ነው
ስለልጇ ብላ ሌላ ህይወት ሳትመኝ በስደት # ተንከራታ ሰው ቤት ደክማ
ለአመታት የሰራችበትን ጨርሳ ዛሬ ልመና ወጥታለች
ምስኪኗ ኢልሀምም ህመሙ ስለባሰባት ትምህርቷን አቋርጣ አልጋ ላይ
ቀርታለች
እናት ሰአዳ # በቸኛ_ልጇ እንድትድንላት ከ2,000,000 (2ሚሊዮን) ብር በላይ
ያስፈልግሻል ተብላለች
ህመሙ ብሶባት አፏ መቁሰል የጀመረውን የአይኔ ማረፊያ መፅናኛዬን
# እባካችሁ_አድኑልኝ ትላለች
የምንችል # በገንዘብ ካልቻልን # በፀሎትና # በሼር
# እናግዛት ለህፃን # ኢልሀም # እንድረስላት
# አካውንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡-
1000444871176-ሰአዳ አብራር(እናት)
# ስልክ፡-
0910346090-ሰአዳ አብራር(እናት)
0912121942-ውብሸት ተካ
0913559189-ሄኖክ ፍቃዱ
0921058425-ኤደን ተክሉ
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድ ያዳርሱ ለኸይር ሰበብ እንሁን
46 views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 15:05:45 የኢስላም ጠላቶች
ከቁረይሽ እስከ አሁን

የእስልምና እየተስፋፋ መምጣት እጅግ ያሳሰባቸው የነበሩ የቁረይሽ ሹማምንት ለሐጅ ከመላው አረቢያ ወደ መካ የሚመጡ ጎሳዎች እስልምናን በዚሁ አጋጣሚ እንዳይቀበሉና መላውን የአረቢያ ምድር እንዳያጥለቀልቀው ይበልጥ አሰጋቸው።

ይህንን መስፋፋቱን ማስቆም እንዳለባቸው አሰቡ። አስበውም እንዴት ማስቆም እንደሚችሉም ለመምከርም ተሰባሰቡ። የረሱል ”ﷺ” ስብእናን የሚያጎድፍ የስም ማጥፋት ዘመቻ መክፈት ሁነኛ መንገድ መሆኑን ከስምምነት ደረሱ።

የበኑ መኽዙም ጎሳ መሪ የሆነው የቁረይሽ ዋና መሪ አል-ወሊድ ኢብን አል-ሙጊራ ለተሰበሰቡት የቁረይሽ ሹማምንት እንዲህ አላቸው፦ "የቁረይሽ ሰዎች ሆይ! የሐጅ ወቅት እየደደረሰ ነው። በመሆኑም የዐረብ ነገዶች ወደዚህ መምጫቸው እየተቃረበ ነው። ሲመጡ ስለባልደረባቹ (ረሱልን ”ﷺ” ማለቱ ነው) መስማታቸው አይቀርም። በመሆኑም ስለርሱ የምንናገረው ተመሳሳይ መሆን ይኖርበታል አለዚያ ነገር ይበላሻል።"

"አቡ ዐብድ ሸምስ ሆይ! ምን መናገር እንዳለብን አንተ ንገረን።" አሉት ተሰብሳቢዎቹ

"የናንተን ሀሳብ መስማት ነው ምፈልገው።" አለ ወሊድ

"ጠንቋይ ነው" ብንልስ አለ አንዱ

አል-ወሊድም ይህንን ሀሳብ ተቃወመ። "ጠንቋዮች የማይጨበጡ ነገሮችን ይለፈልፋሉ። የድምፅ አወጣጣቸውም ይለያል። በመሆኑም ሙሐመድን ጠንቋይ ነው ማለት አሳማኝ አይሆንም።" አላቸው።

"እብድ ነው" ብንልስ አለ ሌላኛው

አል-ወሊድ ይህንንም ሀሳብ ተቃወመ። "ያበዱ ሰዎች በግልፅ ያስታውቃሉ። በመሆኑም ሙሐመድን እብድ ነው ማለት አያሳምንም።" አላቸው።

"ባለቅኔ ነው" ብንልስ አለ ሌላኛው።

"ይህም በፍፁም አሳማኝ አይሆንም።" አለ አል-ወሊድ

እንግዲያውስ አስማተኛ እና ደጋሚ ነው" ብንልስ

"አስማተኛ እና ደጋሚን በድግምቶቻቸው እና በቋጠሮዎቻቸው በሚገባ እናውቃቸዋለን። እርሱ ደጋሚም አስማተኛም አይደለም።" አለ አል-ወሊድ

"ታድያ ምንድነው ብንል ይሻላል?" ሲሉ ተሰብሳቢዎቹ መልሰው አል-ወሊድን ጠየቁት።

እርሱም እንዲህ አለ፦ "በአላህ ይሁንብኝ ንግግሩ ጣፋጭ ነው። የንግግሩ መልዕክት እንደዘምባባ ግንድ ጠንካራ ሲሆን ቅርንጫፎቹም ግሩም የሆኑ የበሰሉ ፍሬዎችን እንደሚያዥጎደጉድ ነው። ስለርሱ ንግግር አሉታዊ ሀሳብ ብትሰነዝሩ ወዲያው ይጋለጥባቹሀል። የሆነው ሆኖ ካቀረባችሁት ሀሳብ "አስማተኛ ነው" የሚለው የተሻለ ነው። ምክንያቱም ሰውን ከአባት እና ከወንድሙ፣ ባልን ከሚስቱ፣ ሰዎችን ከጎሳቸው የመለያየት ችሎታ ያላቸው አስማተኞች ናቸው።"

አላህ ይህንን የቁረይሽን ሴራ አስመልክቶ የቁርዓን አንቀፅ አወረደ። የኢስላም ጠላቶች ያኔም ከተቻለ የእስልምናን ብርሃን ለማጥፋት ካልሆነም የእስልምናን መስፋፋት ለመግታት ያልሸረቡት ሴራ፣ ያልከፈቱት የዘመቻ፣ ያላወጁት የጦርነት ዓይነት አልነበረም። ግና የእስልምና ባለቤት ኃያሉ አምላክ አላህ ነውና እንኳን ሊያጠፉት እጅግ ተስፋፍቶ ዛሬ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በመላው ዓለም ይገኛሉ።

ዛሬ በዚህ ዘመንም የኢስላም ጠላቶች እንደትላንቱ ሁሉ እስልምናን ለማጥፋት ተኝተው እያደሩ አይደለም። እንኳን ሊያጠፉት በነካኩት ቁጥር እጅግ ተስፋፍቶ ዛሬ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች በመላው ዓለም እስልምናን እየተቀበሉ ነው። በፍጥነት እየተስፋፋ ያለ ብቸኛ ሐይማኖት መሆኑንም የገዛ ጠላቶቹ ጥንት አረጋግጧል።
38 views12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 14:56:01
የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌላቭሮቭ አነጋጋሪ መግለጫ እንደዚህ ይላል

" የዩክሬን በሩሲያ መወረር እንቅልፍ ነስቷችሗል ? እንግዲያውስ እንደዚህ አድርጉ ዩክሬይንን እንደ ፍልስጥኤም ውሰዷት ሩሲያን ደግሞ እንደ አሜሪካ በቃ ያኔ ሰላም ትሆናላችሁ "

ይህ የሰርጌ ላቭሮቭ ወይራ የሆነ ንግግር ብዙዎችን አነጋግሯል ። እኔን ሲገባኝ የሚኒስትሩ ገለፃ የአለምአቀፉን ማህበረሰብ ፍርደገምድልነት ያጋለጠ አስመሳይነቱን ያረጋገጠ ነው ።

የእውነት የአንድት ሀገር መወረር ከሆነ እንቅልፍ የነሳችሁ ለምን የፍልስጤም መወረር እንቅልፍ አልነሳችሁም ? ለምን የነርሱ መጨቆንና በጅምላ መገደል አልቆረቆራችሁም ማለቱ ነው ። አዎ የሩሲያ ወረራ ከሆነ እንቅልፍ የነሳችሁ አሜሪካ ያንን ሁሉ ሀገር ወርራ ስታፈራርስ ለምን እንቅልፍ አልነሳችሁም ነበር ? ለምን ያኔ ሚሊዮናት ንፁሃንን ስትጨፈጭፍ አልቆጫችሁም ማለቱ ይመስለኛል ደግሞም እንደዚያው ነው !

እናም አሉ ጉምቱው ፖለቲከኛ ሰርጌ ላቭሮቭ " እናም እንቅልፍ እንዲወስዳችሁ ከፈለጋችሁ ሩሲያን እንደ አሜሪካ ዩክሬይንንም እንደ ፍልስጥኤም ቁጠሯቸው ያኔ ሰላም ትሆናላችሁ !!"

#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
34 views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 21:15:11
ወላሂ በ አስቸኳይ ሼር ይደረግ 2020 ሚባለው ጫማ ከጀርባው የአሏህ ስም አለበት የሃያሉ ጌታችን ስም ነው እየተረገጡ ያለው እባካችሁን አይተን ዝም አንበል

ለበለጠ መረጃወች ለማገኘት
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር
በሊንኩ ይቀላቀሉ
185 views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:32:05 ጥያቄ፤ ኢየሱስ አምላክ ነውን? ኢየሱስ እኔ አምላክ ነኝ ብሎ ነበርን?

መልስ፤ በእርግጥ ኢየሱስ “እኔ አምላክ ነኝ” ብሎ በቀጥታ ስለመናገሩ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ የለም። ይሁን እንጂ ኢየሱስ አምላክ ስለመሆኑ ግን አላወጀም ማለት አይደለም። ለምሳሌ ያህል የኢየሱስ ቃል በዮሐንስ ፲፥፴ እነደተጻፈው እነዲህ ይላል፣ “እኔና አብ አንድ ነን።” ላዩን ሲታይ ይህ አምላክ አንነደሆነ ማወጁን ላያመለክት ይችላል። ቢሆንም፣ ለኢየሱስ ንግግር የአይሁድ አቀባበል ማየት በቂ ነው፤ “አይሁድም፣ ‘የምንወግርህ፣ ተራ ሰው ሆነህ ሳለህ፣ ራስህን አምላክ በማድረግ፣ የስድብ ቃል ስለተናገርህ ነው እንጂ ከእነዚህ ስለ የትኛውም አይደለም’ ብለው መለሱለት” (ዮሐንስ ፲፥፴፫)። አይሁድ የኢየሱስን ንግግር የአምላክነቱን አዋጅ እንደሆነ ገባቸው። በእነዚህ ጥቅሶች ኢየሱስ አይሁድን “እኔ አምላክ አይደሁም” ብሎ አልገሠጻቸውም። ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ አምላክነቱን በእርግጥ ማመኑን ነው፤ “እኔና አብ አንድ ነን” (ዮሐንስ ፲፥፴)። ሌላው ምሳሌ ደግሞ በዮሐንስ ፰፥፶፰ የተጻፈውን ነው፤ “ኢየሱስም፣ ‘እውነት እላችኋለሁ፤ አብርሃም ከመወለዱ በፊት እኔ፣ እኔ ነኝ’ አላቸው።” ለዚህም መልስ አይሁድ ኢየሱስን ሊወግሩት ድንጋይ አነሱ (ዮሐንስ ፰፥፶፱)። አምላክ ነኝ ብሎ መናገሩ እነደስድብ ባይቆጥሩት ኖሮ፣ አይሁድ ኢየሱስን በድንጋይ ሊወግሩት ባልተነሱ ነበር።

ዮሐንስ ፩፥፩ እነደሚለው፣ “…ቃልም እግዚአብሔር ነበር።” ዮሐንስ ፩፥፲፬ እንዲህ ይላል፣ “ቃልም ሥጋ ሆን።” ይህ በግልጽ እነደሚያሳየው ኢየሱስ ሥጋ የለበሰ አምላክ ነው። የሐዋሪያት ሥራ ፳፥፳፰ እነደሚነግረን፣ “…በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ጠብቁ።” ማነው ቤተ ክርስቲያንን በደሙ የዋጃት? ኢየሱስ ክርሰቶስ። የሐዋሪያት ሥራ ፳፥፳፰ ላይ እነደተጻፈው፣ ቤተ ክርስቲያንን በገዛ ደሙ የዋጃት አምላክ ነው። ስለዚህም፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ነው!

የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ቶማስ ኢየስሱን አስመልክቶ እንዲህ ሲል ተናገረ፣ “ጌታዬ፤ አምላኬም!” (ዮሐንስ ፳፥፳፰)። ለዚህ ንግግሩም ኢየሱስ ቶማስን ሲያርመው አይታይም። ቲቶ ፪፥፲፫ የጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት በርትተን እንድንጠብቅ ይመክረናል (በተጨማሪም ፪ኛ ጴጥሮስ ፩፥፩ ማየት ይቻላል)። በዕብራውያን ፩፥፰፣ አብ ስለ ኢየሱስ እንዲህ ይላል፤ “ስለ ልጁ ግን እንዲህ ይላል፤ ‘አምላክ ሆይ፤ ዙፋንህ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ጸንቶ ይኖራል፤ ጽድቅም የመንግሥትህ በትር ይሆናል።”

በራእይ እንደተጻፈው፣ መልአክ ሐዋሪያው ዮሐንስን እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አዘዘው (ራእይ ፲፱፥፲)። በወንጌል እነደሚነበበው፣ ኢየሱስ ብዙ ጊዜ አምልኮ ይቀበል ነበር (ማቴዎስ ፪፥፲፩፤ ፲፬፥፴፫፤ ፳፰፥፱፣ ፲፯፤ ሉቃስ ፳፬፥፶፪፤ ፲፱፥፲)። ሰዎች ሲያመልኩትም አልገሠጻቸውም። ኢየሱስ አምላክ ባይሆን ኖሮ ግን፣ እኔን አታምልኩ ባለ ነበር፤ ልክ መልአኩ ሐዋሪያው ዮሐንስን እነዳዘዘው። ስለ ኢየሱስ አምላክነት የሚመሰክሩ ጥቅሶችና የወንጌል ገጸ ንባቦች ብዙ ናቸው።

ከሁሉም የላቀ ምክኒያት ግን አለን። ይኸውም ኢየሱስ አምላክ ባይሆን ኖሮ፣ በሞቱ የምድርን ሐጢአት ቅጣት መቀበል ባልቻለ ነበር (፩ኛ ዮሐንስ ፪፥፪)። አምላክ ብቻ ነው ለዚህ መጨረሻ ለሌለው ቅጣት ለመቀበል (፪ኛ ቆሮንቶስ ፭፥ ፳፩)፣ ለመሞትና ከሙታን በመነሳትም ሞትንና ሐጢአትን ማቸነፍ የሚችለው።
34 views11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:17:18 ተክቢር

አሏሁ አክበር!
የክርስትና መምህራን በጥላቻ ቀን ከሌሊት ኢሥልምናን ያጠለሻሉ፥ የእነርሱ የጥላቻ ዲስኩር እጅ እጅ ያላቸው እና ከጉያቸው የነበሩት የኦርቶዶክስ ምእመናት ወደ ዲኑል ኢሥላም እየመጡ ነው። 15 ልጆች ወደ ዲኑል ኢሥላም በሸሀደተይን ገብተዋል። የእኛ መምህራን የተውሒድን ብርሃን ለሙሥሊሙ እና ሙሥሊም ላልሆነው እያስተማሩ ይገኛሉ እንጂ አሉታዊ ነገር ላይ አይጠመዱም። አሏህ ይህንን ዲን ከፈለገ በከሃዲያንም ቢሆን ያጠናክረዋል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነሆ ሙሥሊም የሆነች ነፍስ እንጂ ሌላው ጀነትን አይገባትም፥ አላህ ይህንን ዲን ከፈለገ በከሃዲያንም ቢሆን ያጠናክረዋል"። ﻋَﻦْ ﺃَﺑِﻲ ﻫُﺮَﻳْﺮَﺓَ، ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗَﺎﻝ ﻋﻦ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲّ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﺃﻧﻪ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳَﺪْﺧُﻞُ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻧَﻔْﺲٌ ﻣُﺴْﻠِﻤَﺔٌ، ﻭَﺃَﻥَّ ﺍﻟﻠﻪَ ﻳُﺆَﻳِّﺪُ ﻫَﺬَﺍ ﺍﻟﺪِّﻳﻦَ ﺑِﺎﻟﺮَّﺟُﻞِ ﺍﻟْﻔَﺎﺟِﺮِ‏

መጪው ዘመን የኢሥላም ነው።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
26 views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:11:16 ●አንብቦ # በእስላም የተማረከው # የአሜሪካ ታዳጊ!!
➥ # ከክርስቲያን ቤተሰቦች ተወልዶ # እናቱ የፈለገውን እምነት ራሱ ይምረጥ
ብላ የተለያዩ የሀይማኖት መፅሀፎችን አምጥታለት ራሱ አንብቦ # እስልምናን
የመረጠው ህፃን!!
➥ # አሜሪካዊው ህፃን # አሌክሳንደር_ፍሪትዝ ከክርስቲያን ወላጆች በ1990
ዓ.ም ተወለደ። እናቱ ከመጀመሪያው ጀምሮ የራሱን ሀይማኖት እንዲመርጥ
ወሰነች ከተለያዩ # ሀይማኖቶች የተውጣጡ የሀይማኖት # መጽሃፍቶችን
አመጣችለትና መፅሃፎችን ካነበበ በኋላ በ8 አመቱ # እስልምና መቀበሉን
አስታወቀ።
➥እራሱን # ሙሀመድ_አብደላህ ሁሌም በሚወዷቸው በነብዩ ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም ስም ነው የሰየመው..!!
በአንዱ ኢስላሚክ ቻናል በእናቱ ታጅቦ ቀረበ .. አቅራቢው ታዳጊውን ጥያቄ
ሊጠይቅ በዝግጅት ላይ ነበር ነገር ግን አስቀድሞ የፕሮግራም አቅራቢውን
የጠየቀው ጥያቄ አቅራቢውን አስገረመው .. እንዴት # ሀጅ እና # ዑምራን
አደርጋለሁ ብሎ ነበር ታዳጊው የጠየቀው።
➥ጉዞው ውድ ነው # የኢህራም ልብስ የት ነው የምገዛው? ታዳጊው
በትምህርት ቤቱ ጎበዝ ነበር የሶላት ጊዜ ሲደርስ ብቻውን ቆሞ # የሰላትን ጥሪ
# አዛን ካደረገ በኋላ ሶላቱን ብቻውን ይሰግድ ነበር።
➥የፕሮግራም አቅራቢው ጋዜጠኛ እንዲህ ሲል ጠየቀው፡ በዚህ ጉዳይ ላይ
ችግር ወይም እንግልት ያጋጥምሃል?
በቁጭት መለሰ አንዳንድ ጊዜ ሶላት ያልፈኛል ምክንያቱም ዘመኑን ስለማላውቅ
ነው..!!
➥ጋዜጠኛው፡- ወደ # እስልምና የሳበህ ምንድን ነው? እሱም መለሰ፡- ስለ እሱ
ባነበብኩ ቁጥር የበለጠ ወደድኩት።
➥ጋዜጠኛው፡- ምኞቶችህ ምንድን ናቸው?
ታዳጊው ልጅ በሚያስገርም መለሰ፡- ሁለት ምኞቶች አሉኝ...
የመጀመርያው፡ የሙስሊሞችን ትክክለኛ ምስል ማንነት ለአለም ማሳወቅና የኔን
ተወዳጅ ነብዩ ሙሀመድን(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ገጽታ የሚያበላሹ የአሜሪካ
ፊልሞች ሆኑ ግለሰቦች ስለ ነብዩ መሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እውነተኛ
ገፅታ እንዲያውቁ ማድረግ።
➥ሁለተኛው፡ ወደ # መካ ሄጄ የጥቁር ድንጋይን መሳም እመኛለሁ። ረመዳንን
ትፆም ነበርን??
እሱም መለሰ፡- አዎ..ባለፈው አመት.. አባቴ እንደማልችል ተገዳደረኝ ነገር ግን
መፆሜን ሲመለከ በጣም ተገረመ!!
➥ጋዜጠኛው - ሌሎች ምኞቶችህ ምንድን ናቸው? እሱም እንዲህ ሲሉ መለሰ፡
# ፍልስጤም ወደ ሙስሊሞች ትመለስ ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ ይህ መሬታቸው
ነውና ከነርሱ በሀይል በኢስራኢዎች ተነጥቃለች...!!
➥ጋዜጠኛው፡- ከወላጆችህ ጋር # የአሳማ ሥጋ ትበላለህ?
እሱም መለሰ፡- አሳማው በጣም የቆሸሸ እንስሳ ነው..እኔ አልበላውም, እና
ሰዎች እንዴት እንደሚበሉት አላውቅም..!!
➥ጋዜጠኛው፡- በትምህርት ቤት ትሰግዳለህ?
እሱም መለሰ፡- አዎ በየእለቱ የምሰግድበት # ቤተ መጽሐፍት ውስጥ ድብቅ
ቦታ አለ።
➥ሰዓቱ የመግሪብ ሰላት ደርሷልና ወደ ፕሮግራም አቅራቢ ተመለከተና፡-
# የሰላትን ጥሪ አዛን እንዳደርግ ትፈቅድልኝ አለውና ተነስቶ የአዛን ጥሪውን
አደረገ፣ የፕሮግራሙ አቅራቢ # አይኖች በእንባ ሞሉ።
Ibn Ahmed
25 views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:05:26
ይሄ የለዬለት ፅንፈኛ አሸባሪ ደብተራ እንደፈለገ እዬተንቀሳቀሰ በአማራ ክልልና በአዲስ አበባ ሙስሊሞች ያለምንም ምክኒያት ከመንገድላይና ከስራ ቦታቸዉ እየታፈኑ ለእስር እየተዳረጉነዉ።አሁንም እንላለን የፍትህ ያለህ ዛሬም ነገም እንጠይቃለን ፍትህህህህህ ለኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች
28 views11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ