"የኔልሰን ማንዴላ .. ☞ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው ። ስሙም ፒተር ይባላል ። አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ማንዴላ በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ ። ዘረኛው ፒተርም "አቶ ማንዴላ! አሳማና ወፍ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" አላቸው ፣ ብልሁ ማንዴላም " አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብሏቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ ። በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል። አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ .... ►"ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው ቦርሳ ብር በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ ጥበብ ቢኖር በቅድሚያ የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ ማንዴላን ጠየቀው ፣ ►ማንዴላም "ገንዘቡን አወስደዋለሁ" ብሎ መለሰለት ። ►ፕሮፌሰሩም በግልምጫ " አንተ ሞኝ ነህ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ አወስድ ነበር" አለው፣ ►ማንዴላ ፈገግ እያለ" ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው ። በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ ደደብ ብሎ ይፅፋል ። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ ደደብ የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ ፣ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ " ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ፃፍልኝ" @WubTarikoch 1.3K views _U_K_I, edited 05:49