2022-08-30 19:17:41
#ATTENTION
ኮምቦልቻ !
የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ምክር ቤት የከተማድን ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ከመከረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል ፦
- ከዛሬ ነሀሴ 24/2014ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከ11 ጀምሮ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- በማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም አላስፈላጊ ህዝብን ወደ አለመረጋጋት የሚወስዱ የተዛቡ መረጃዎችን መልቀቅ በህግ ያስጠይቃል።
- በከተማው አሉባልታ ማናፈስ በህብረተሰብ መካከል ሽብርና ውዥንብር የሚነዙ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ እንዲጠየቁ ተወስኗል።
- በከተማ ደረጃ አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች እስከ 11 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።
- ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተንተርሶ የከተማችን ነዋሪ ላይ ያለ አግባብ ዋጋ ጭማሪ በማድረግ እና ሸቀጦችን በመከዘን በገበያ ላይ እጥረትን በመፍጠር ነዋሪውን ለተጨማሪ ወጭና የኑሮ ጫና የሚጥሉ አካላት ላይ ህጋዊ እረምጃ እንዲወሰድ ታዟል።
- በምግብ ቤቶች ፣ መጠጥ ቤቶች፣ ካፌዎችና ግረሶሪዎች ከ11 ስዓት ጀምሮ ማንኛውም አገልግሎት መሰጠት ተከልክሏል።
- DSTV ማሳያ ቤቶች ፣የቡና መሸጫ ቤቶች ፣የሺሻና የጫት ማስቃሚያ ቤቶች ውስጥ ተሰብስቦ ጫት መቃም በህግ ያስጠይቃል።
- የአልጋ አከራ ሆቴሎች፣ የመኖሪያ እና መደብ አከራዮችን አገልግሎት ሲሰጡ የተገልጋዩን ማንነት የሚገልፅ መረጃ በመያዝ አገልግሎት እንዲሰጡና መታወቂያ ኮፒ ማድረግ እንዳይዘነጉ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
ለመረጃ እና ጥቆማ፦ በስልክ ቁጥሮች 0335510005
0335510945
0921038804 ላይ መደወል ይቻላል።
@tikvahethiopia
792 views16:17