Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Times

የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitatimes — Wolaita Times W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wolaitatimes — Wolaita Times
የሰርጥ አድራሻ: @wolaitatimes
ምድቦች: ጤና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.99K
የሰርጥ መግለጫ

Proving Media and Advertising Service

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 17:32:41
349 views14:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:32:17 የዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የቆዩ ባለ ልዩ ተሰጥኦ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን አስመረቀ

በዩኒቨርሲቲ አዲስ ከተቋቋሙ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት አንዱ ነው- STEM (የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ) ማዕከል።

ማዕከሉ በ2014 ዓ.ም STEMpower ከተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ካምፓስ የተቋቋመ ነው።

የዩኒቨርሲቲው STEM ማዕከል ከድርጅቱ በተገኘ የ 8.7 ሚሊየን ብር ድጋፍ የተሟላ የኮምፒዩተርና የኤሌክትሮኒክስ ላብራቶሪዎችን በተደራጀ መልኩ አካቶ ይዞ ይገኛል።

በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሂሳብ (STEM) ትምህርቶች ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ተኮር ትምህርት በማሰልጠን ቴክኖሎጂና ፈጠራን ማስፋፋት የማዕከሉ ግብ እንደሆነ ከማዕከሉ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

የዩኒቨርሲቲው STEM ማዕከል ነሐሴ 4/2014 ዓ.ም በዎላይታ ዞን ሶዶ ከተማ እና ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ካሉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 50 ባለ ልዩ ተሰጥኦ ተማሪዎችን ተቀብሎ አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ታውቋል።

በማዕከሉ ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የቆዩት 50 ሥልጠናቸውን በሚገባ መከታተላቸው ተረጋግጦ በዛሬው ዕለት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ፥ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ፣ ዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ውብዓለም ግርማ፥ የፋይናንስ ዳይሬክተር ተክሉ መና እና ሌሌች የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል።

በተማሪዎቹ የምረቃ ሥነ ስርዓት መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዶ/ር ውብዓለም ግርማ በበጋ ዕረፍት ወቅት ማዕከሉ ነሐሴ 4/ 2022 በወላይታ አካባቢ ላሉ የሶዶ ከተማ እና ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች 50 ተማሪዎች ተቀብሎ ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።

በኮምፒዩተርና ኤሌክትሮኒክስ ላብራቶሪዎች ውስጥ የSTEM ትምህርት ለመቅሰም ከተመለመሉ 50 ተማሪዎች ውስጥ 27 ወንድ እና 23 ሴት ተማሪዎች እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

የዩኒቨርሲቲው STEM ማዕከል በመጀመሪያው ዙር የከተማ አቀፍ ፕሮግራሙ ከዎላይታ ዞን ሶዶ ከተማ እና ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 50 ተማሪዎችን ተቀብሎ የተሟላ የመኝታ እና የምግብ አገልግሎ በመስጠት መጀመሩን ዶ/ር ውብዓለም ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ ለአንድ ወር ትምህርታቸውን በሚገባ ሲከታተሉ መቆየታቸውን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ በዛሬው ዕለትም ለምረቃ በቅተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ማዕከሉ ለቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ትልቅ አቅም ይፈጥራል ያሉት ዶ/ር ውብዓለም፤ በቀጣይ ተማሪዎች የፈጠራ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ በስፋት እንሰራለን ብለዋል።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ ማዕከሉ የሳይንስ ዕውቀትና ዝንባሌ ያላቸውን ወጣት ተማሪዎችን ከንድፈ ሃሳብ በተጨማሪ በተግባር የተደገፈ እውቀት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ለሰልጣኝ ተማሪዎች ነገ የፈጠራ እና ሳይንስ ባለቤት እንድትሆኑ የሚያስችላችሁን ተግባር ተኮር ዕውቀትና ክዕሎት በመቅሰማችሁ እድለኞች ናችሁ ሲሉም ተናግረዋል ዶ/ር መስፍን።

ዩኒቨርሲቲው ለመማር ማስተማር እና ፈጠራ ስራ መጎልበት በቀጣይም በተለየ መልኩ እገዛ ያደርጋል ሲሉም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ በበኩላቸው ለሰልጣኞቹ ሁሌም ራዕይ ኖሮን የሳይንስ ልማት እውን እንዲሆን ሁላችንም በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

ለውጥ ማምጣት ካለብን ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥ ዘርፉን በሰው ኃይልም ሆነ በግብዓት በመደገፍ ለሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እድገት በትብብር እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

በቀጣይ ዓመት በተለየ መልኩ በርካታ ተማሪዎችን ተቀብለን ለማሰልጠን እና ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ዕድገት ጥረት የሚያደርጉ ተማሪዎችን ተቀብለን ለማሰልጠን ከወዲሁ ዝግጁ ነን ሲሉም ፕ/ር ታከለ ተቁመዋል።

ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በማዕከሉ ስለነበራቸው ቆይታ እና ቀጣይ መኖር ስላለበት አግባባዊ የትምህርት እና ስልጠና ግንኙነት ላይ ለነሱት ጥያቄ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።

የዩኒቨርሲቲው አመራሮች በማዕከሉ የሚገኘውን የተደራጀ የኮምፒዩተርና የኤሌክትሮኒክስ ላብራቶሪዎችን ጉብኝት አድርገዋል።
የWT ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ
ዌብሳይት፡ wolaitatimes.com
ቴለግራም፡ https://t.me/WolaitaTimes
WT መዝናኛ፦ https://www.facebook.com/WT-መዝናኛ-105588772237484/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/wolaitatime/
ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/channel/UCQy9hoOijiE8FStts2SmtXw
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/wolaitatimes/
344 views14:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:57:09
452 views10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:56:52 "የተቃጣብንን የጠላት ወረራ እየመከትን የልማት ስራችንን እናስቀጥላለን" - አቶ እርስቱ ይርዳው

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው በዎላይታ ዞን በ1ሺሄ/ር መሬት ላይ በግል ባለሀብት ጥረት እየለማ ያለ የበቆሎ ምርጥዘር ማባዥ ጎብኝተዋል

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው በወላይታ ዞን በዱግና ፋንጎ ወረዳ በአቶ ዳኜ ዳባ እየለማ ያለ የበቆሎ ምርጥ ዘር ብዜት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት የተቃጣብንን የጠላት ወረራ በአስተማማኝ ሁኔታ እየመከትን የልማት ስራችንን እናስቀጥላለን ብለዋል።

ለክልሉ አርሶ አደሮች አስፈላጊዉን የበቆሎ ምርጥ ዘር ለማቅረብ በግል ባለሀብቶች እና በሌሎች አካላት መጠነ ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ አካባቢው የልማት ስራዎችን ለመጎብኘት በመጡበት ወቅት የግብርና ስራው በስፋት እንዲካሔድ የሰጡትን አስተያየት መነሻ በማድረግ ባለሀብቱ የጀመሩትን የግብርና ኢንቬስትመንት እንዲያስፋፉ መደረጉን ጠቁመዋል።

በባለሀብቱ እየተባዛ ያለው ምርጥ ዘር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ፋይዳው ከፍተኛ እንደሆነ የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በተያዘው የምርት ዘመን እስከ ከ50ሺ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር እንደሚያስገኝም አብራርተዋል።

ባለፈው ዓመት በቤኒሻንጉል ክልል ምርጥ ዘር ሲባዛ እንደነበር የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በአካባቢው በተከሰተ የጸጥታ ችግር ምርቱን መሰብሰብ ሳይቻል መቅረቱን አስታውሰዋል።

ዘንድሮ በክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀም በራስ ሀይል ምርጥ ዘር የማባዛት ስራ እየተሰራ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ከበቆሎ በተጓዳኝ በቦለቄ፣ በስንዴ፣ እንዲሁም በስራ ስር ሰብሎችም ምርጥ ዘር የማባዛት ስራ በስፋት እየተካሔደ ነው ብለዋል።

ወራሪው እና ሽብርተኛው የህወሀት ቡድን ባለፉት 30 ዓመታት በስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ በዜጎቻችን ላይ ከፍተኛ ስቃይ ካደረሰው ተግባር ባሻገር የሽብር ቡድኑ ከስልጣን ሲገለል ደግሞ በሀገሪቱ ግልጽ ወረራ በመፈጸም በዜጎች ላይ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ዘግናኝ ጭፍጨፋ መፈጸሙን አውስተዋል።

የሽብር ቡድኑ ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በማበር ሀገሪቱ የጀመረችው የልማት ጉዞ እንዲደናቀፍ በአማራና በአፋር ክልሎች ወረራ በመፈጸም ዜጎችን ለስቃይ እየዳረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የሽብር ቡድኑን እኩይ ተግባር መላው የክልሉ ህዝብ ድርጊቱን ከማውገዝ ባለፈ ከጥምር ጦሩ ጋር የበኩሉን ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም የክልሉ ህዝብ ለጥምር ጦሩ ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በዎላይታ ዞን በልዩ ልዩ የግብርና ኢንቬስትመንት የተሰማሩት አቶ ዳኜ ዳባ እንዳሉት ዘንድሮ ወደ 1ሺ ሄክታር በሚጠጋ መሬት ላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በማባዛት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

እንደ አቶ ዳኜ ገለጻ ከአትክልትና ፍራፍሬ እርሻ በተጓዳኝ የክልሉን የምርጥ ዘር ፍላጎት ለማሟላት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

የእርሻ ስራው ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር ከማድረጉም ባለፈ የሀገሪቱን የምርጥ ዘር ፍላጎት እስከ 20 በመቶ ለመሸፈን እየሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል።

የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ በበኩላቸው ግብርናውን ለማዘመን ከሚተገበሩ ስራዎች ውስጥ አንዱ የምርጥ ዘር አቅርቦት ተቀዳሚ ነው ብለዋል።

ባለፈው አመት ከአየር ጠባይ ለውጥ እና በጸጥታ ችግሮች ሳቢያ በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ጠቁመዋል።

ባለፈው ዓመት ያጋጠመውን ችግር መነሻ በማድረግ በክልሉ ሁሉንም አማራጮችን በመጠቀም ምርጥ ዘር እየተባዛ መሆኑን አውስተዋል።

ሀገሪቱ ለ3ኛ ጊዜ በሽብር ቡድኑ በተወረረችበት ጊዜ ሉዓላዊነታችንን ከማስጠበቅ በተጓዳኝ የልማት ስራዎችን አቀናጅቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ህብረተሰቡም የሀገርን ደህንነት ለማስጠበቅ እየሰጠ ያለው ምላሽ ከፍተኛ እንደሆነም አቶ ተስፋዬ ተናግረዋል።
440 views10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:27:58
434 views13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:27:20 የኦሞ ባንክ ዎላይታ ሶዶ ዲስትሪክት ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ

ባንኩ በይፋ ወደ ባንክ ዘርፍ ከተቀላቀለ በኃላ የመጀመሪያውን ዓመታዊ ጉባዔ የላቀ አፈፀምና እና በተነፃፃሪነት ዝቅተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ መዋቅሮችን በመለየት ውይይት በማካሄድ በጥንካሬና በድክመት የተነሱ ጉዳዮችን “ሁለንተናዊ ለውጥ ለላቀ አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ዓመታዊ ጉባኤ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገምግሟል።

በዕለቱ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊሰ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንደገለፁት "ወደ ባንክ ባደረግነው ሽግግር ከእኛ ጋር የነበሩ የተቋማችን ደንበኞች ከኦሞ ባንክ ጋር ደንበኝነታቸውን አጠናክረው በመቀጠል የባንክና አነስተኛ የብድር አገልግሎቶችን ጭምር በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ይደረጋል" ብለዋል፡፡

ባንኩ በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተጨማሪ በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የብድር አቅርቦት በተቀላጠፈ መንገድ በመዘርጋት እስከ ገጠር ድረስ የሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎችን በፍትሀዊነት ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያስችለው ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

ተቋም በዘንድሮው በጀት አመት የተጣራ 322 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማግኘት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ የተሳካ ቁጠባ ማስቆጠብ መቻሉንና ከ3.4 ቢሊዮን ብር በላይ ብር ለስራ ዕድልና ሌሎች ብድር ፈላጊዎች ማሰራጨቱን በመግለፅ፥ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ላይ የበኩሉን አውንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኦሞ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊስ አብራርተዋል።

በባንኩ ካሉ አጠቀላይ ድስትሪክቶች መካከል የተሻለ አፈፃፀም 1ኛ ደረጀ ያስመዘገበው የዎላይታ ሶዶ ድስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን ያይና እንደተናገሩት ተቋሙ በበጀት አመቱ ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ ከደንበኞች ቁጠባ ያስቆጠበ ሲሆን ከ596 ሚሊየን ብር በላይ ብድር ማሰራጨቱንና ለተለያዩ ጉዳዮች ብድር ከወሰዱ ደንበኞች ከ554 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር ማስመለስ መቻሉን አብራርተዋል።

አቶ ተመስገን ያይና "ባንክ ሆነናል ብለን አንቀመጥም ነገር ግን ለደንበኞቻችን እርካታ ብዙ መስራት አለብን በማለት ባንኩን በቴክኖሎጂ ከማዘመን አኳያ ይበልጥ መስራት እንዳለብንና ከሌሎች ባንኮች ጋር ተወዳዳሪና ለብዙ ደንበኞቻችን የተሻለ አገልግሎት መስጠት ይጠበቅብናል" ብለዋል፡፡

ተቋሙ ዓላማውን ለማሳካት የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጎ የስራ አቅጣጫው ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሮ በ2014 በጀት አመት በተግባር አፈፃፀማቸው የላቀ ውጤት በማስመዝገብ 1ኛ ሶዶ ዲስትሪክት፣ 2ኛ ወልቂጤ ዲስትሪክት እና 3ኛ ሆሳዕና ዲስትሪክት ከቅርንጫፍ 1ኛ ዎላይታ ሶዶ ዳሞታ 2ኛ ሚሻ እና 3ኛ አበሽጌ በመሆናቸው የዋንጫ፣ የሜዳሊያና የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷቸው ጉባኤው ተጠናቋል፡፡

ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ !!
የWT ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ
ዌብሳይት፡ wolaitatimes.com
ቴለግራም፡ https://t.me/WolaitaTimes
WT መዝናኛ፦ https://www.facebook.com/WT-መዝናኛ-105588772237484/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/wolaitatime/
ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/channel/UCQy9hoOijiE8FStts2SmtXw
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/wolaitatimes/
438 views13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:28:05 ኦሞ ባንክ ከባንክ አገልግሎት በተጨማሪ ከዚህ በፊት ይሰጥ የነበረው የማይክሮፋይናንስ አገልግሎቶችን ሳያቋርጥ መቀጠሉ በአጭር ጊዜ ውጤታማ ተቋም እንደሚያደርገው የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ገለፁ

ባንኩ በይፋ ወደ ባንክ ዘርፍ ከተቀላቀለ በኃላ የመጀመሪያውን ዓመታዊ ጉባዔ የላቀ አፈፀምና እና በተነፃፃሪነት ዝቅተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ መዋቅሮችን በመለየት ውይይት በማካሄድ በጥንካሬና በድክመት የተነሱ ጉዳዮችን “ሁለንተናዊ ለውጥ ለላቀ አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ዓመታዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገምግሟል።

በባንኩ ካሉ አጠቀላይ ድስትሪክቶች መካከል የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገበው የሶዶ ድስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን ያይና እንደተናገሩት ተቋሙ በበጀት አመቱ ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ ከደንበኞች ቁጠባ ያስቆጠበ ሲሆን ከ596 ሚሊየን ብር በላይ ብድር ማሰራጨቱንና ለተለያዩ ጉዳዮች ብድር ከወሰዱ ደንበኞች ከ554 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር ማስመለስ መቻሉን አብራርተዋል።

ሌሎች ከወልቅጤ ድስትሪክት የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ እና ከሲዳማ ክልል አስተያየት የሰጡ ስራአስኪያጆቹ ተቋሙን ዘመናዊ በማድረግ ከዚህ በፊት ለደንበኞች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ተደራሽና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደረገው ሽግግር የበለጠ ስኬታማ እንደሚያደርግ ገልጿል።

የስራ ኃላፊዎቹ ለባንኩ ውጤታማነት ከመቸውም ጊዜ በላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

ተቋም በዘንድሮው በጀት አመት የተጣራ 322 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማግኘት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ የተሳካ ቁጠባ ማስቆጠብ መቻሉንና ከ3.4 ቢሊዮን ብር በላይ ብር ለስራ ዕድልና ሌሎች ብድር ፈላጊዎች ማሰራጨቱን በመግለፅ፥ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ላይ የበኩሉን አውንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኦሞ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊስ ለ"ዎላይታ ታይምስ ሚዲያ" አብራርተዋል።

ባንኩ በተለይም በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተጨማሪ በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የብድር አቅርቦት በተቀላጠፈ መንገድ በመዘርጋት እስከ ገጠር ድረስ የሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎችን በፍትሀዊነት ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያስችለው ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

ኦሞ ባንክ በአገር አቀፍ ደረጃ ካሉት ባንኮች ጋር ተወዳዳሪ በመሆን ከዚህ በፊት ስሲጥ የነበረው የማይክሮ ፍይናንስ አገልግሎት ሳያቋርጥ በተጨማሪ የባንክ አገልግሎት ላይ ይበልጥ ውጤታማነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ በየአካባቢው የሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ቦታዎችን በዘመናዊ አሰራርና አደራጃጀት መልሶ የማደራጀት ተግባር ተጠናክሮ በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑም አቶ አለማየሁ አስረድተዋል።

በመድረኩ የኦሞ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊስ፣ የኦሞ ባንክ ቦርድ አባላት፣ የክልሉ እንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብረጋ ብራሃኑ ጨምሮ ከሲዳማ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልልና ከደቡብ ክልል ፍርድቤት ፕረዚዳንቶች፣ ከሁሉም ድስትሪክቶችና የየቅርንጫፎች ስራ አስኪያጆች እንዲሁም የክልል፣ የሀላባ ዞን ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ተሳታፊ ሆኗል።

ተቋሙ የአገልግሎት አድማሱን በየጊዜው በማስፋት ዓላማውን ለማሳካት በተለይም ሀገሪቱ በፋይናንስ ዘርፍ እያካሄደች ባለው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት የድርሻውን በማበርከት የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተቋሙ ወደ ባንክነት በይፋ በመቀላቀሉ ተግባር ዙሪያ ውይይት ተደርጎ የስራ አቅጣጫው ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሮ ዲስትሪክቱ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎች ማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ጉባኤው ተጠናቋል።

የWT ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ
ዌብሳይት፡ wolaitatimes.com
ቴለግራም፡ https://t.me/WolaitaTimes
WT መዝናኛ፦ https://www.facebook.com/WT-መዝናኛ-105588772237484/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/wolaitatime/
ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/channel/UCQy9hoOijiE8FStts2SmtXw
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/wolaitatimes/
629 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:14:10
ኦሞ ባንክ ወደ ባንክ አገልግሎት በይፋ ከተቀላቀለ በኃላ የመጀመሪያውን ዓመታዊ ጉባዔ እያካሄደ ነው።

የኦሞ ባንክ የ2014 ዓ.ም ዕቅድ
አፈጻጸም ግምገማና የ2015 ዓ.ም ዕቅድ
ዝግጅት “ሁለንተናዊ ለውጥ ለላቀ
አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ዓመታዊ ጉባኤ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ኑሪዬ ባንኩ የሚያካሂደው ታሪካዊ ጉባኤ በዞኑ መሆኑ ዕድለኛ ያደርጋል ብለዋል።

ተቋም ከ24 ዓመት በፊት በትንሽ ካፒታል ተቋቋመው በአሁኑ ወቅት ወደ ባንክ ከመሻገር በተጨማሪ በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ላይ የበኩሉን አውንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኦሞ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊስ ገልጸዋል።

ባንኩ በተለይም በሀገሪቱ ፍይናንስ ዘርፍ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተጨማሪ በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የብድር አቅርቦት በተቀላጠፈ መንገድ በመዘርጋት እስከ ገጠር ድረስ የሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎችን በፍትሀዊነት ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያስችለው ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

ተቋሙ የአገልግሎት አድማሱን በየጊዜው በማስፋት ዓላማውን ለማሳካት በተለይም ሀገሪቱ በፋይናንስ ዘርፍ እያካሄደች ባለው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት የድርሻውን በማበርከት የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተቋሙ ወደ ባንክነት በይፋ በመቀላቀሉ ተግባር ዙሪያ ውይይት ተደርጎ የስራ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ የኦሞ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ኃ/ጊዮርጊስ፣ የኦሞ ባንክ ቦርድ አባላት፣ ከሁሉም ድስትሪክቶችና የየቅርንጫፎች ስራ አስኪያጆች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
718 views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:25:47 "ለመልካም አስተዳደር ችግሮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለሠላማዊ መማር ማስተማር መረጋገጥና መዝለቅ እጅ ለእጅ ተያይዘን በትብብር እንስራ" ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ

በዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ስር የሚገኙ 14 ዳይሬክቶሬቶች የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ ያተኮረ ግምገማ ተካሄዷል።

በመድረኩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ታከለ ታደሰ በአፕላይድ ሳይንስ ምድብ የሚገኘው ዩኒቨርሲቲያችን በ2022 ዓ.ም የጤና እና ግብርና ልዕቀት ማዕከል ለመሆን የሰነቀውን ራዕይ ዕውን ለማድረግ በትብብርና በቁርጠኝነት መስራት መቻል አለብ ብለዋል።

እያንዳንዱ ዘርፍ ተቋምን የሚያሻግር እና ሕብረተሰብን ተጠቃሚ ሊያደርግ የሚችላ ዕቅድ በማዘጋጀት ውጤት ሊያመጣ በሚያስችል መልኩ ተግባራዊ ሊያደርግ ይገባል ነው ያሉት ፕ/ር ታከለ።

ዩኒቨርሲቲው በ2014 እንደ ተቋም ውጤታማ እንዲሆን በትብብር በተሰራው ስራ የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥ፣ ችግር ፈቺ ጥናት እና ምርምር እንዲጎለብት፣ አሳታፊ የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት ተግባር እንዲስፋፋ የዘርፉ ዳይሬክተሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ ፕሬዝዳንቱ አመስግነዋል።

በቀጣይ ጊዜያትም ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፣ ለችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር መጎልበት፣ ለአሳታፊ የማህበረሰብ አገልግሎት መስፋፋት፣ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት መዘመን ሁሉም አካላት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በትጋት መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

በ2015 በጀት ዓመት የትምህርትና ምርምር ጥራትን የማረጋገጥ፤ ዘላቂ ሰላም ልማትን የማስፈን፤ የሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ የማሻሻል እና የማዝለቅ፤ መልካም አስተዳደርን የማስፈን፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን የማዘመን እንዲሁም የድጋፍ፣ ክትትል፣ አመራርና ዕውቅና የመስጠት ተግባራት ትኩረት ይሰጣቸዋል ሲሉ ፕ/ር ታከለ አሳውቀዋል።

ለመልካም አስተዳደር ችግሮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት፥ ብልሹ አሰራሮችን በሕግ አግባብ በአስቸኳይ በማረም እንዲሁም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋይ በመስጠት ለሠላማዊ መማር ማስተማር መረጋገጥና መዝለቅ እጅ ለእጅ ተያይዘን በትብብር እንስራ ሲሉ ፕሬዝዳንቱ መልዕክት አሰተላልፈዋል።

በተቋም ደረጃ በ2015 ዓ.ም ሊተገበሩ የታቀዱ አበይት ሥራዎች መሬት ወርደው ውጤት እንዲያመጡ እና መላውን ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ የበለጠ ተግተና እና ተባብረን እንስራ ሲሉም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል።

በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ስር 14 ዳይሬክቶሬቶች የሚገኙ ሲሆን፤ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም ለ2015 በጀት ዓመት ያዘጋጁትን እቅድ አቅርበው አስተችተዋል።

እያንዳንዱ የዘርፉ ዳይሬክተር በአጭር ግዜ ውስጥ ለቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች ዕቅድ በማውረድ ለተፈጻሚነቱ ተገቢው ድጋፍና ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል።
የWT ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ
ዌብሳይት፡ wolaitatimes.com
ቴለግራም፡ https://t.me/WolaitaTimes
WT መዝናኛ፦ https://www.facebook.com/WT-መዝናኛ-105588772237484/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/wolaitatime/
ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/channel/UCQy9hoOijiE8FStts2SmtXw
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/wolaitatimes/
743 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:59:00
በደቡብ ክልል ጋሞ ዞን ስልፕንግ ሲክኔስ የተባለ አዲስ በሽታ መከሰቱ ተገለፀ

አፋጣኝ የህክምና እርዳታ ካልተገኘ የሰው ልጆችን በህይወት የመቀጠል ጉዳይ እጅግ ፈታኝ ያርገዋል ወይም ገዳይ ነው የተባለለት በሽታ Human Africa Trypanosomiasis (sleeping sickness) መከሰቱን የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ባካሄደው የሳምንታዊ ውይይት አስታውቋል።

በአሁኑ ወቅት Human Africa Trypanosomiasis (sleeping sickness) ክስተት በጋሞ ዞን በቁጫ አልፋ ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሸጥ ከሆኑ ቀበሌያት ወደ ሰላምበር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በወባ በሽታ ተጠርጥረው ለህክምና በመጡ ታካሚዎች ላይ በተወሰደ ናሙና ውጤቱን ለማወቅ ተችሏል ብሏል፡

በመሆኑም በክልሉ በየትኛውም አካባቢዎች መሰል የህመም ምልክቶች ክስተት ዙሪያ በህረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ እየተፈጠረ መሄድ ስላለበት እና በተለይ አሁን ክስተቱ በተፈጠረባቸው አከባቢዎች ጋር አጎራባች የሆኑና አና በማህበራዊ ትስስር የሚገናኙ ሁሉም ቀበሌዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በየአከባቢው ባሉ የጤና መዋቅር በአስቸኳይ ሪፖርት እንዲደረግ ጥሪውን ኢኒስቲትዩቱ አቅርቧል፡፤

በአገራችን ትኩረት የሚሹ አሩራማ በሽታዎች ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር ከዓለም ጤና ድርጅት እና ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ድጋፍ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት እና ከጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች በተቋማትና በማህበረሰብ አቀፍ እየተከናወኑ እንደሚገኝ የክልሉ ጤና ቢሮ አሳውቀዋል።
@wolaitatimes
695 views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ