2022-08-29 14:23:19
━━━━━━━━━━━━━━━━
ሴትን አላምንም
ክፍል 10
ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ
መኪናውን ወደዳር አቁሜ ስመለከት ቴክስቱ የአህላምዬ ነው። ተጣድፌ ከፈትኩት
ሰኢዲዬ?
… የሳቅ ረሀብተኛ ዘወትር አልቃሽ ሴት ሁኜ ነበር የተገናኝነው ፤ ያሳለፍኩት ህይወት ጨላልሞብኝ የህይወት ለዛው ጠፍቶብኝ ስባክን እና ስብከነከን ቆሜ እንዳልራመድ አቅም ያጣው ሆኜ ሳለው ነው መጥተህ የህይወትን ቀጣይ አቅጣጫ ያሳየህኝ እህቴ ለኔ ከምንም በላይ ነበረች። ከእርሷ ውጪ ህይወት ሞት መስሎ በሚታየኝ ሰአት ድንገት የህይወትን ብርሃን አብርተህ አሳየኝህኝ "ሁሉም ሰልፈኛ ነው ተራውን ጠባቂ "ያልከኝ ምክር እህቴን አስታወሰኝ አህላምዬ "ሰው ታመመ ብለሽ ብዙ አትጨነቂ ሁሉም ሰው ዛሬ ባይታመም ነገ ፣ ዛሬ ባይሞት ነገ ይሞታል የተራ ጉዳይ ነው ስለዚህ ለሚመጣው የህይወት ፈተና እራስሽን አዘጋጂ" ትለኝ ነበር።
እርሷም ተራዋን ጠብቃ ሄደች ፤ ግን አንተን ተክታልኝ የሄደች መስሎ እንዲሰማኝ አደረግከኝ። እውነት በጠፋበት ዘመን የእውነት ሰው ሆነህ አሳይተህኛል ፤ በእጆችህ የነካሃቸው እግሮቼ ፣ ከጉድጓድ ውስጥ በእቅፍህ ያወጣህበት የትህትና ጥግ ፣ ወንድሜን ተክተህ ከቤት ወደ ት/ቤት ያመላለስክበት ስብእናህ ከልቤ የሚጠፋ አይደለም ፤ ዛሬ ደግሞ ከመራራው ሀዘን መለስ ብዬ እንዳስብ ረድተህኛል ለዚህም ከልቤ አመሰግናለው ከትምህርት ቤት የቀርሁባት ያቺ ቀን እህቴ በጠና ታማ ስለ ነበር ነው።
ነግቶ እስከማይህ ናፍቆቴ ብዙ ነበር ጥላዬ መስለህ ትታየኛለህ አደራ ከጐኔ ሁነህ አበርታኝ………። ከአህላም የተላከው መልእክት ነበር
" እውነተኛ ሳቅ እና ደስታ ውስጤ ሲፀርስ ተሰማኝ… እሷን የእኔ አድርጌ አሰብኳት መላ አካለቴ ጆሮ ሆኖ ስለእርሷ ማዳመጥ ፈለገ ፣ ሁለመናዬ የእርምጃዎቿን ኮቴ ማዳመጥ ጀመሩ።
ተስፋ ጭንቅት እንዲሁም ፍቅር አንድ ላይ ተዋህደው ነፍሴን በፍቅር ውቅያኖስ ውስጥ ሲከቷት ታየኝ… አህላምን ሊወስዳት የመጣው ችግር ሲወረፍ ታየኝ… … ምን ያህል በፍቅሯ እውር እንደሆንኩኝ ባየች ብዬ አስብ ነበር ፤ ዛሬ ግን የፍቅርን ጭላጭ ሳትጐነጨ አልቀረችም ቴክስቷ ለኔ ከምንም በላይ ዋጋ ነበረው… … የአንድ አንድ ሰው ኖሮም ሞቶም ጠቃሚነቱ ጉልህ ነው።
የአህላምዬ እህት ሞታ የሚወዋዳዱ ሰዎችን ህይወት ግን አስቀጠለች ፤ ህልሜን በእውኑ አለም ውስጥ ያገኝሗት መስሎ ታየኝ። ማለዳ የወፎችን ድምፅ በእቅፌ ውስጥ ገብታ ስታዳምጥ… በፍቅር ስንወዳደስ ፣ በፍቅር ስንጐራረስ ፣ በአንድ የህይወት ጣራ ውስጥ ህይወትን አብረን ስንቃኝ ታየኝ እና ፈገግ አልኩኝ።
ስልኬን አውጥቼ መልእክቴን አኖርኩላት……
አህላምዬ ከልብ አመሰግናለው እውነታው ይህ ነው………ልቤ በአንቺነትሽ ሀሴት ተሞልታለች አንቺ በህይወቴ ምዕራፍ ከመጣሽ ጊዜ ጀምሮ አዲስ ተስፋ እና አዲስ ሃይል አግኝቻለው … አይኖቼም በድካም አይፈዙም ራስ ምታትም ሆነ ነስር ከዛች ልዩ ቀን በሗላ ተመልሶ አያውቅም ሀኪሜ ሁነሽ አዳንሽኝ ፈዋሼ ሁነሽ የመኖር ህልሜን በእጥፍ ጨመርሽው።
አህላምዬ?
ልቤ ዘወትር ስላንቺ ያስባል ፣ አይኖቼ አንቺን ብቻ ለማየት ያማትራሉ ፣ ጉልበቶቼ ወደ አንቺ
ለመጓዝ ይበረታሉ ፣ በልቤ ዙፋን ነግሰሽ ተሞሽረሻል ………… ። መልእክቴ ተቋጨ "አፈቅርሻለው" ብዬ ላፍረጥርጠው? አዎ አፍቅርያታለው እሷን ወደ ህይወቴ ካመጣሁኝ ቡሗላ አይበርደኝም ፣ አይጠማኝም ከምግብ የበለጠ የሚያጠግበኝ፣ ከመጠጥም ይልቅ የሚያረካኝ፣ ፍቅሯ በውስጤ አለ። "እነዚህ ቃላቶች ሁሉ የኔ ቢሆኑም ፍቅሬን አይገልፁልኝም " ግን አሁን አፈቅርሻለው አልላትም"። ለሁሉም ጊዜ አለው።
የመኪናዬ በር ተንኳኳ …… አንዲት ላይዋ ደምቆ ውስጣ ግን አንዳች የመሸነፍ ስሜት የተላበሰች ሴት ነበረች "ሴተኛ አዳሪ"። "ማልወደው ቃል"
መስኮቱን ዝቅ ሳረገው ሳልናገር ፈጥና ወንድሜ ቦታውን ልቀቀው እንጂ የስራ ቦታ ነው ከፈለግክ አንዳችንን ይዘህን ሂድ ካልሆነ ተንቀሳቀስ አለች ቆጣ ብላ።
እሺ ብዬ መኪናዬን አስነስቼ ሄድኩኝ አሳዘነችኝ ግን ደግሞ ምን ታድርገው ። የረከሱ ወንዶች የገንዘባቸው መለኪያ የስሜታቸው ማርኪያ አድርገዋቸዋል ሴትን ልጅ እንዴት ለርካሽ ነገር ይጠቀሟታል?
ሴትን ልጅ "ከእንብርቷ በታች ላለው አካሏ ሳይሆን ከአንገቷ በላይ ስላለው ጭንቅላቷ ብሎ የሚቀርብ ወንድ ከተማው ላይ የለም እንዴ"? የሴትነትን ዋጋ ያላወቁ ወንዶች ከስሜታቸው ቀድሞ ለህሊናቸው ቢያስቡ ምን አለ? አንዲትን ሴት ወደ መልካም ህይወት መምራት ከመከራ ህይወት ማውጣት የህሊና እረፍት እንጂ ሌላ ምንን ይሰጣል ?
እነዚህ ስጋ ነጋዴዎች! ሴትን አረከሷት አልኩኝ አንድ የግጥም ስንኝ ትዝ እያለኝ
የሌሊት ስጋ ቤት
ይሄ ስጋ መሸጥ ያተርፋል እያሉ
ያዋጣል እያሉ
የቀን ሳያንሳቸው
እራፊ አሻርጠው ማታም ይወጣሉ
ስጋ እየተስማማው ስጋ እያጣፈጡ በላተኛው ሁሉ
ቀን የበሬ ገዝተው
ባዋዜ አዋህደው ፤
ሲቆርጡ እየዋሉ
ሲጠብሱ እየዋሉ
ማታም እየጠጡ
ነፍሳቸውን ስተው
የሰው ስጋ ገዝተው
ዝሙት ይሰራሉ ፤
የበሬን ጥብስ ጥጋብ
ፀሀይ እንደገባች በሰው ያበርዳሉ፡፡ አልኩኝ ።
በተደጋጋሚ እነ አህላምዬ ጋር በለቅሶው ሰበብ መሄድ አብዝቻለው ፤ አንዳች የመቀራረብ ስሜት ሁለታችንም ላይ ይታያል…… መመላለሴን ያዩና ስወጣ ከአህላምዬ ጋር የሚመለከቱኝ እየታዘቡኝ መስሎ ታየኝ "በፍቅሯ ሽባ ልፍልፍልስና ጠውላጋ ነው ብለው ያሙኝ እየመሰለኝ ፈራ ተባውን ተያይዤዋለው።
ይበሉዋ ደግሞ ምን ገዶኝ ልክ አይደሉ እንዴ ? በማላዘው አይኔ እየናፈቀችኝ ፣ በከደንኩት አይኔ ደግሞ እያየሗት አይደል? ቃል ባጣው ምላሴ አልሰብኳትም ፣ በድን አካለቴ እሷን አላለም ? የእርሷ ምርኮኛ ነው ቢሉ ምን ተሳሳቱ? ………… ዛሬ ከሌላው ጊዜ የበለጠ አምሽቻለው አህላምዬ መኪና ድረስ ልሸኝህ ብላ አብራኝ ወጥታለች… ፈገግታዋ እየተመለሰ ፍንድቅድቅ ሁና እያተየችኝ ነው "አልሃምዱሊላህ" የሁለት ሰው ደስታ ተመለሰ የእኔም ፣ የእርሷም "በኔ ውስጥ እሷ አለቻ"………… አስፓልቱ ዳር ቆመን ስለ ቤተሰብ እያወራን እርሷም መበርታት እንዳለባት እያወራን አንድ መኪና ከላይ እየተመዝገዘገ መጣ…………እጇን ስቤ ወደ ደረቴ አስጠጓሇት መኪናው አለፈ ፤ እኔና እሷ............
ክፍል አስራ አንድ ይቀጥላል……
━━━━━━✦✗✦━━━━━━━
ምርጫዎ ስለሆነ እናመሰግናለን
209 viewsEyoba, 11:23