Get Mystery Box with random crypto!

Tesfa

የቴሌግራም ቻናል አርማ tesfaevent — Tesfa T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tesfaevent — Tesfa
የሰርጥ አድራሻ: @tesfaevent
ምድቦች: ጥቅሶች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.66K
የሰርጥ መግለጫ

አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው?
እግዚአብሔር አይደለምን?

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-01-17 12:00:55
እግዚአብሔር አምላክ ለአንተ ታማኝ ነው። ለቃሉ ሁሌም ታማኝ ነው። ዓላማውን ሁሉ ለመፈጸም ታማኝ ነው።  በፍፁምነቱ ሁሉ ታማኝ ነው። እግዚአብሔርም በሥራው ሁሉ ይህ ነው።  በፍፁምነቱ፣ በፃድቅነቱ፣ በመንገዱም ታማኝ አምላክ ነው።  ህይወቶቻችሁን ለእርሱ በመስጠት እርሱ ዓለት ይሆንላችሁ ዘንድ ትፈልጋላችሁ?
ልንረዳችሁ ዝግጁ ነን @tesfa_mentor


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
225 views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 12:00:07
እስከዛሬ ድረስ እንደ አይን ብሌን ተጠንቅቆና ተንከባክቦ እዚህ ያደረሰን አምላክ አለን! በምናልፍባቸው ሁኔታዎቻችን እንደሰው ስናስበው ምንም እንኳን እግዚአብሔር አብሮነት የሌለ ቢመስለንም ነገር ግን እስከዛሬ ድረስ ባለፍንባቸው ነገሮች ሁሉ እንደምንፈልገው አድርጎ እያስተማረን እያበረታን እርሱ ብቻውን እይመራን እና እየተንከባከበን እኛ እንዳሰብነው ሳይሆን እሱ እንዳሰበልን ሆኖ እዚህ አድርሶናል ከዚህም በሃላ በሚኖረን እድሜ እስከዛሬ ድረስ የተጠነቀቀልን አምላክ ያሰበልን እና ያየልን ቦታ ላይ በክንፎቹ አዝሎ ያደርሰናል።
ወደዚህ ወደ ሚመራው፣ ወደ ሚጠብቀው አምላክ እንቅረብ ፤ ይህ ካልሆነ ልንረዳችሁ ዝግጁ ነን @tesfa_mentor

መልካም ሳምንት ይሁንላችሁ!
#tesfa #hope #brightmonday

#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
298 views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 10:40:09 ደስ ብሎኛል!
ኢየሱስ ስለተወለደልኝ!

ልደቱ ልደቴ ስለሆነ!
በእርሱ የእግዚአብሔር ፅድቅ ስለሆንኩ!
የሰላም አለቃ ስላለኝ!
መድኃኒት ስለተወለደልኝ!

ነገር ግን ይሄን ሁሉ ደስታ

በበረት የተወለደው ኢየሱስ በልባችን ካልተወለደ አይጠቅመንም!
እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ ፈጥሮታል፡፡ ሰው ሁሉ በሃጢያት ወድቋል፡፡ ሁሉም ሰው የእእግዚአብሔር ፍጥረት ነው፡፡ ሁሉም ሰው ግን የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም፡፡ ወይም ኢየሱስ ስለሰዎች ሁሉ በመስቀል ላይ ሊሞት በምድር ላይ ስለተወለደ ብቻ ሰው ሁሉ ከመቀፅበት የእግዚአብሔር ልጅ አይሆንም፡፡ የብቻ የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን መመዘኛ አለው፡፡ ለእግዚአብሔር ፍጥረት ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን ብቸኛው መመዘኛ ኢየሱስን መቀበል ነው፡፡

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
በበረት የተወለደው ኢየሱስ በልባችን ካልተወለደ አይጠቅመንም፡፡ ሃይማኖተኛ ልንሆን እንችላለን፡፡ ብዙ ነገሮችን ለእግዚአብሔር ብለን ልናደርግ እንችላለን፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሰራልንን ለእኔ ነው ብለን ኢየሱስን በመቀበል ዳግመኛ ካልተወለድን ግን የኢየሱስ በምድር ላይ መወለድ አይጠቅመንም፡፡ ኢየሱስን ያደንቀው ለነበረ ኒቆዲሞስ ለተባለ የህግ መምህር ኢየሱስ ያለው ይህንን ነው፡፡
ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ዮሃንስ 3፡3፣5

በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ገናን በፍቅር ልናከብረው እንችላለን፡፡ ኢየሱስን ከልባችን ልናደንቀው እንችላለን፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ በልባችን ካልኖረ ወደ ምድር የመጣበትንና ከብፅዕት ድንግል ማርያም የተወለደበትን አላማ ስተነዋል፡፡
ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። ዮሃንስ 1፡21
ኢየሱስ በምድር ላይ ስለተወለደ ብቻ ከመቀፅበት አንድንም፡፡ ኢየሱስ ስለተወለደ ብቻ ሰዎች ከመቀፅበት የሚድኑ ቢሆን ኖሮ ኢየሱስ ለፍጥረት ሁሉ ወንጌልን ስበኩ ብሎ ባላዘዘን ነበር፡፡ የምስራቹን ቃል ሰምተው የሚያምኑ ብቻ ናቸው የሚድኑት፡፡
እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ማርቆስ 16፡15-16
የሚድኑት ኢየሱስን እንደ አዳኝ የተቀበሉ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ የምንም ሃይማኖት ተከታዮች ስለሆንን ብቻ አንድንም፡፡ ከሃጢያት የሚያድነን ኢየሱስን እንደ አዳኝና ጌታ አድርገን መቀበላችን ብቻ ነው፡፡
በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሃንስ 3፡16
ሰዎች በየእለቱና በየደቂቃው ኢየሱስን እየተቀበሉና እየዳኑ ነው፡፡ እኛ ግን ኢየሱስን ወደ ልባችን ሳናስባውና በልባችን ሳይወለድ ኢየሱስ በምድር ላይ ስለተወለደ ብቻ ድነናል ብለን ካሰብን ተታለናል፡፡ የኢየሱስ መወለድ እንዲጠቅመን ወንጌልን ማመን ይጠበቅብናል፡፡ የሚያድነን የእግዚአብሔር ሃይል የኢየሱስ ስለሃጢያታችን መሞቱን የምስራች ማመን ነው፡፡
በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ሮሜ 1፡16

#ደስብሎኛል

change your profile with #ደስብሎኛል frame
use @add_frame_bot
share with ur friends!

ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይህን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
1.4K views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 10:40:08
968 views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 10:25:01
ደስ ብሎኛል! መድኃኒት ተወልዶልኛል! #day_5

የሰውን ልጅ ከኃጢአታቸው ለማዳን የተላከ የእግዚአብሔር ልጅ ነው።ኢየሱስ!
ከነብያት ሰምተው ለሺህ አመታት የዚህን አዳኝ መወለድ ሲጠብቁ ለነበሩ ሁሉ የምስራቹን እንዲያበስሩ፤ መልአኩም ለእረኞች ተገልጦ የምሥራቹን ነገራቸው። እነርሱም መንጎቻቸውን ትተው የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግደውን አዳኙን ሕፃን አይተው ደስታን አበሰሩ፤ አዳኙን ነገሩ። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢያታችን ስለላከልን፣  በራሳችን ቅጣቶቻችንን እንድንሸከም ስላልተወን፣ ይልቁንም ከእርሱ ጋር እንድንታረቅ ልጁን ስለሰጠን፣  መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ስለተወለደልን   እድለኞች ነን።
ወዳጄ ሆይ ክርስቶስ በህይወትህ  እንዴት መድኃኒትህ እንደሆነ ለማወቅ በእርሱ ማመን እና በእርሱ መኖር አለብህ። እናም እሱ ስለተወለደ እና መሞትን ስለመረጠ፣ የመዳንን ስጦታ እንደተቀበልክ እርግጠኛ መሆን ትችላለህ። ዋናው ማድረግ ያለብህ እርሱን እንደ ግል ጌታህ እና አዳኝህ አድርገህ መቀበል ብቻ ነው። ደስ ይበላችሁ!  ክርስቶስ መድኃኒት ተወልዶላቿል!
#ደስብሎኛል

change your profile with #ደስብሎኛል frame
use @add_frame_bot
share with ur friends!

ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይህን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
1.2K views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 09:20:01
ደስ ብሎኛል! የሰላም አለቃ ስላለኝ #day_4
ከእግዚአብሔር ጋር በሰላም እንድንኖር ብቸኛው ምክንያት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 
ሰውን ከኃጢአት ባርነት እና ከዘላለም ሞት  የሚያድነው ምንም አይነት መልካም ስራ እንደሌለ እግዚአብሔር አስቀድሞ ስለሚያውቅ  የእግዚአብሔር ፍፁም በግ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን  ከድንግል ማሪያም እንዲወለድ አደረገ። 
በእርሱም የሚያምኑ ሁሉ በሰላም እንድንኖር ኢየሱስ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ ወደ ምድር መጣ።
"ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፥ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።  ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።  ( ኢሳይያስ 9:6 )
የኢየሱስ ስም በብዙ ተገልጧል። ከዚህም ውስጥ  የሰላም አለቃ  ነው። ሰላም ከሌለ የህይወት ቀጣይነት ሊኖር አይችልም።  የእግዚአብሔር ልጅ የነገሥታት ንጉሥ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደፈጠረው ዓለም ስጋን ለብሶ የመጣው ለዚሁ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ሊያደርገን።
ደስ ብሎኛል የሰላም አለቃ ተወልዶልኛል።
#ደስብሎኛል

change your profile with #ደስብሎኛል frame
use @add_frame_bot
share with ur friends!

ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይህን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
980 viewsedited  06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 07:17:17 Tesfa pinned a photo
04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 12:00:38
change your profile with #ደስብሎኛል frame
use https://t.me/add_frame_bot
share with ur friends!

ሰው ለመሆኑ ከዙፋኑ ለመውረድ ምክንያቱ እኔ ነኝ።  እርሱ የሆነውን ሁሉ ማዳኑም፣ ክብሩም፣ ውርደቱም፣ የኖረው ኑሮ ፣የተጎሳቆለው፣  የሰራው ተአምር ፣ ሁሉ ለእኔ ነው። ስለዚህ ልደቱ ልደቴ ነው።  ጊዜ ማይገድበው ነገርግን በተገደበ ቦታ ክብር በሌለበት በበረት ስለተወለደልኝ ልደቱ ልደቴ ነው። ይሄን ሁሉ የሆነው እኔን እያሰበ በእኔ ምክንያት ነበር። እናም ልደቱ ልደቴ የሆነው ስለእኔ የተደረገልኝን በማሰብ ውስጥ ነው።  ልደቱን ከምንም ጋር አላያይዘውም። መድኃኒቴ፣ እረኛዬ ጌታዬ ስጋ የለበሰበት ያ! ጊዜ ለእኔም ልደቴ ነው። ለተቀበሉት በስሙ ላመኑት ለእነርሱ የልጅነት ስልጣን እንደሰጣቸው ሁሉ ዛሬም አንተ በስሙ ብታምን የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ስልጣን ይኖርሀል። ልደቱንም በእሩቅ እንደ ባህል ከማክበር ይልቅ የልደቱን ጌታ በማወቅ እና ልደቱ ልደትህ እንደሆነ በመረዳት ትኖራለህ።
ደስ ብሎኛል!

ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይህን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
3.7K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 11:33:02
#day_3
እግዚአብሔር ጻዲቅ ነው የእግዚአብሄርን ፊት ማየት የሚቻለው በጽድቅ ነው። ጽድቅ ፊቱን ታያለች ከጽድቅ ውጪ የእግዚአብሔር ፊት አይታይም፤ የእግዚአብሔር የጽድቁ አካል መሆን አይቻልም። ነገር ግን የእግዚአብሔር ጽድቅ ደግሞ በልጁ በኢየሱስ ነው። “አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤” (ሮሜ 3:21-22)
ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ህግ ማሟላት፣ የእግዘብሔርን ፍላጎት ማሟላት ግድ ይላል፤ ያንን ሊያደርግ የሚችል ደሞ ንጹህ ኃጢአት የማያውቀው ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ ኃጢአታችን ኃጢአተኛ ሳይሆን ኃጢአት ያደረገውን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ መሞት ነበረበት፤ “እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።”(2ኛ ቆሮ 5፥21) ስለዚህ ይህንን ይሆን ዘንድ ግን ግዴታ በረት ውስጥ መወለድ ነበረበት። እናም በእርሱ የእግዚአብሔር ፅድቅ ሆነናል። ስለዚህ የእሱ በበረት መወለድ የእኛን የእግዚአብሔር ጽድቅ የመሆናችን የምስራች ማብሰሪያ ቀን ነው።
ደስ ብሎኛል!
#ደስብሎኛል #tesfa


ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይህን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
807 viewsedited  08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 10:30:01
ደስ ብሎኛል! ልደቱ ልደቴ ነው። #day_2
ሰው ለመሆኑ ከዙፋኑ ለመውረድ ምክንያቱ እኔ ነኝ።  እርሱ የሆነውን ሁሉ ማዳኑም፣ ክብሩም፣ ውርደቱም፣ የኖረው ኑሮ ፣የተጎሳቆለው፣  የሰራው ተአምር ፣ ሁሉ ለእኔ ነው። ስለዚህ ልደቱ ልደቴ ነው።   ጊዜ ማይገድበው ነገርግን በተገደበ ቦታ ክብር በሌለበት በበረት ስለተወለደልኝ ልደቱ ልደቴ ነው። ይሄን ሁሉ የሆነው እኔን እያሰበ በእኔ ምክንያት ነበር። እናም ልደቱ ልደቴ የሆነው ስለእኔ የተደረገልኝን በማሰብ ውስጥ ነው።  ልደቱን ከምንም ጋር አላያይዘውም። መድኃኒቴ፣ እረኛዬ ጌታዬ ስጋ የለበሰበት ያ! ጊዜ ለእኔም ልደቴ ነው። ለተቀበሉት በስሙ ላመኑት ለእነርሱ የልጅነት ስልጣን እንደሰጣቸው ሁሉ ዛሬም አንተ በስሙ ብታምን የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ስልጣን ይኖርሀል። ልደቱንም በእሩቅ እንደ ባህል ከማክበር ይልቅ የልደቱን ጌታ በማወቅ እና ልደቱ ልደትህ እንደሆነ በመረዳት ትኖራለህ።
ደስ ብሎኛል!
#ደስብሎኛል #tesfa


ደስ ያለው ሰው ሼር በማድረግ ይሀን የደስታ ምክንያት ለሌሎች እናጋራ!
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | Tiktok | Youtube
4.5K viewsedited  07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ