በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር የተመራ የከፍተኛ ኃላፊዎች ልኡካን ቡድን በዛሬው ዕለት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚገኘውን የኩባንያችንን የኤክስፒሪየንስ ማዕከል ጎበኘ፡፡ ለልዑካን ቡድኑ በማዕከሉ በቀረበው ዓውደ-ርዕይ የሀገራችንን የቴሌኮም አገልግሎት ጉዞ እንዲሁም ኩባንያችን ለማህበረሰባችን፣ ለቢዝነሱ እና ለተቋማት የሚያቀርባቸው ዲጂታል ሶሉሽኖችን ላይ በተግባር የተደገፈ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ በመጨረሻም ኩባንያችን በገነባው ሰፊ መሰረተ ልማት በመጠቀም የዲጂታል ሶሉሽኖችን በስፋት በማቅረብ በማሕበረሰባችን ሕይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያመጣ እንዲሁም የተቋማት እና ቢዝነሶች አሰራር በማዘመን ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የማድረጉን ጉዞ ለማፋጠን የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ተገልጿል፡፡ #Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia 18.2K views15:09