Get Mystery Box with random crypto!

ባህርዳር ነበር የቀረቻቸው ባህርዳር ከተማን ዛሬ ሌሊት እንደ የመን ከተሞች ሲያፈራርሷት አድረዋል፤ | Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

ባህርዳር ነበር የቀረቻቸው ባህርዳር ከተማን ዛሬ ሌሊት እንደ የመን ከተሞች ሲያፈራርሷት አድረዋል፤ አሁንም ከቱርክ እና ከምዕራባውያን ተገዝተው በመጡ ዘመናዊ መሳሪያዎች እየፈራረሰች ነው። ከትናንት ከሰዓት ጀምሮ ሙሉ አደሩን እስካሁን በተለይም ቀበሌ 14 የጦር አውድማ ሆኗል። በዐማራ ህዝብ ላይ ይፋዊ ጄኖሳይድ ታውጇል።
ንፁሐን እንደ ቅጠል እየረገፉ ናቸው። 14 እሸት ፓርክ አካባቢ ብቻ ከ50 በላይ የንፁሐን አስክሬን የሚያነሰው ጠፍቶ ወድቋል። እናት በሯ ላይ የተገደለውን ልጇን አልቅሳ መቅበር አቅቷ ቤት ውስጥ እስክሬን አስቀምጣ ብቻዋን ደረቷን እየደቃች ነው።

ይህ "ኦሮሙማ" የተሰኘ አይዲዮሎጂ የሚከተል ፀረ-ዐማራ፣ ፀረ-ኢትዮጵያዊ፣ ፀረ-ሃይማኖት፣ ፀረ ሰው የሆነ አገዛዝ ታሪካችንን በማጠልሸት በምናባዊ ልቦለድ እንደ አኖሌ እና ጨለንቆ ያለ የጥላቻ ሐውልት ሰርቶብናል። ያለስማችን ስም ሰጥቶናል። የራሱን ግፍ ደብቆ ግፈኛ አድርጎናል። ነ*ፍ*ጠ*ኛ፣ መጤና ሰፋሪ" እያለ ከክልሉ አፈናቅሎናል።

ዛሬም ይህ ኃይል በፅንፈኝነት ፈርጆ እያሳደደን ነው። ትናንት በወለጋ ገድሎን አልረካም። ከመተከል አሳዶን አላቆመም። "ከዚች ምድር እናጠፋችኋለን" (We Will Erase You From This Land) በሚል መመሪያ ክልሉ ላይ ወረራ ፈጽሟል። እቤታችን ድረስ መጥቶ መትረየስ ደግኖ እየጨፈጨፈን ነው። ሱሪ ለብሶ መንገድ ላይ የሚንቀሳቀሰውን ሁሉ እንደ ቀይ ሽብር በይፋ እረሽነው የሬሳ ኤግዚቪሽን እያሳዩ ናቸው።

ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut