Get Mystery Box with random crypto!

#ሼር_ፖስት! 'እኔም ፋኖ ነኝ' ኢንተርኔት በመዝጋት የህዝብን ድምጽ በማፈን የሚካሄድን የህዝብ ጭ | Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

#ሼር_ፖስት! "እኔም ፋኖ ነኝ" ኢንተርኔት በመዝጋት የህዝብን ድምጽ በማፈን የሚካሄድን የህዝብ ጭፍጨፋ በጽኑ እቃወማለሁ"

-"ይህ ጦርነት ተራ ጦርነት አይደለም። ልክ እንደ አይሁዳውያን ከምድረገጽ እንዲጠፋ የተፈረደበት ታላቁ ዐማራን በመሰረታት ሐገር አንገቱን ደፍቶ እንዳይኖር የሚደረግ የመጨረሻው ትግል ነው። ይህ ትግል ከቀያቸው አፈናቅለው ከቀየው ሊያፈናቅሉት የመጣን ኃይል የማክሸፍ ትግል ነው"

እንደዚህ ያሉ መልዕክቶችን በሜሴጅ ለ10 እና ለ15 ሰው ሼር በማድረግ እንድታስተላልፉ አደራ ለማለት እወዳለሁ።

-የትናንቱ አጠቃላይ ዝርዝር መረጃ።

-ባህርዳር ከትናንት ጀምሮ መንገዶች ሁሉ ዝግ ናቸው። ከሰዓት ቀበሌ 14 ልደታ ማርያም አካባቢ ከፍተኛ ተኩስ የነበረ ሲሆን፣ የኦህዴድ ብልፅግና ሠራዊት የቆሎ ተማሪዎችን ጨምሮ 6 ንፁሃንን ገድሏል። በተመሳሳይ ቀበሌ 13 በተለምዶ ገጠር መንገድ ላይ በፓትሮል ይንቀሳቀሱ የነበሩ የአገዛዙ ሠራዊቶች ወርደው ሁለት ወጣቶችን ተኩሰው አውራ ጎዳና ላይ ገድለዋል። ሥርዓተ ቀብራቸው እዛው 13 በዓታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።

-ልደታ ማርያም ላይ በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከ10 በላይ የአብይ አሕመድ ኮማንዶዎች ተማርከዋል።

-አገዛዙ መኮድን፣ ኤርፖርቱንና አሚኮን ለመከላከል በየቦታው ታንክ ጠምዷል። ለምሳሌ ገጠር መንገድ ላይ ታንክ ጠምዷል። መንገዱ ሁሉ ስለተዘጋጋበት ከጎርጎራ በጀልባ ወደ ባህርዳር ከተማ ኃይል እያስገባ ነው። ትናንት ምሽት በሁለት አውሮፕላኖችም አራግፏል። በተመሳሳይ ባህር ዳር ስታዲዬም ውስጥ የመሸገ የመከላከያ ኃይል አለ። ይህ በእንዲህ እያለ አሁንም የአማራ የብልፅግና ካድሬዎች ማታ ላይ ወጣቶችን በመጠቆም ሲያሳስሩ እንደነበር ታውቋል።

-ጎንደር ትናንት ከፍተኛ ችግር የነበረው ማረሚያ ቤቱ ላይ ነበር። ጠባቂ ፖሊሶች ከ20 በላይ ታራሚዎችን ተኩሰው ገድለዋል።

-አዲስአበባ የአማራ ተወላጆች ብቻ እየታሰሩ ይገኛሉ። ትምህርት ቤቶች ሞልተው አዲስአበባ እስታዲየም ታጉረዋል።

ድል ለዐማራ ህዝብ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!



ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut