Get Mystery Box with random crypto!

#ሼር_ፖስት! ጀግኖቻችን ጉብዬና ሮቢትን ተቆጣጥረው ወደፊት እየተመሙ ናቸው። ይህ ጦርነት ከአማራ | Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

#ሼር_ፖስት! ጀግኖቻችን ጉብዬና ሮቢትን ተቆጣጥረው ወደፊት እየተመሙ ናቸው። ይህ ጦርነት ከአማራና ከአፋር ክልል ወጥቶ በራሳቸው ሜዳ መሆን አለበት የሚል የፀና አቋም አለኝ። ሚስኪን ወገኔ ድጋሜ መፈናቀል፣ የርዳታ ድርጅቶች ጦረተኛ መሆን የለበትም። ሞትና ስደት ይበቃዋል።

ይህ የሚሆነው ግን መከላከያን፣ ልዩ ኃይሉንና ግምባር ላይ እየተዋደቁ ያሉ ፋኖዎችን ስንደግፍና ስናበረታታ ነው።

በጣም አሳዝኖኝ ያመሸው ደግሞ በህብረት ወያኔን የገጠመውን መከላከያ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ ሆነው ሳለ ፋኖዎችን ብቻ ነጥለው ለማጀገን የሄዱበት እርቀት ነው። በርግጥ ዋና ዓላማቸው ህዝባዊ ኃይሉ እንዳይናበብ፣ ርስበርሱ እንዲጠራጠርና እንዲጣላ በእጅ አዙር ወያኔን የማገዝ ሥልታዊ ዘዴ ናት። ከዚህ በፊትም ብየዋለሁ ወያኔ ከጦርነቱ በፊት ድጅታል ሚዲያውን እንዴት መቆጣጠር እንዳለበት አስልቶና አሰማርቶ ነው ውጊያ የጀመረው። አሁንም በተግባርም እያየን ያለነው ይሄንኑ ነው።

ነርገርግን መከላከያ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ አንድም ሦስትም ናቸው፤ አይነጣጠሉም፤ በጋራ ይወጋሉ፥ የጋራ መሰዋእትነት ይከፍላሉ፥ በአንድ ጉድጓድ ይቀበራሉ። ድል ሲያደርጉ ድሉ የጋራ ነው፤ ሽንፈት ሲያጋጥም ሽንፈቱም የጋራ ነው። ድል ሲገኝ ለአንድ ወገን ብቻ በመስጠት በአንድ ግምባር ተሰልፈው የሚዋጉ ወንድማማቾችን ለመነጣጠል የሚደረገው ሴራ ተቀባይነት የለውም።

ሌላው ....ወያኔን የዘንባባ ዝንጣፊ እያነጠፉ፥ ቄጤማ እየነሰነሱ ለመቀበል ሲያለቀልቁ የነበሩ ባንዳዎች ተመትቶ ወደኋላ በመመለሱ ተበሳጭተዋል። አንዳንዶቹ "ውሸት ነው" ብለው ለማሳመን ፀጉራቸውን ሲነጩ ነው ያመሹት። እኔ መረጃ ከምንጩ ቀድቼ እንጂ የማመጠው በስማ በለው ተሳስቼ ሰውንም የማሳሳት ጅል አይደለሁም። የሰማችሁትንም መረጃ ቀጥታ እንደመጣ አላምጨ አልውጠውም፤ ቢያንስ ከሦስት ጊዜ በላይ ክሮስ ቼክ አደርጋለሁ። የምትናደዱ ሰዎች እግዜር ይሁናችሁ። እንደዚህ ከመናደድ በይፋ ወያኔን ተቀላቅላችሁ ብትዋጉ ይሻላችሁ ነበር።