Get Mystery Box with random crypto!

#ሼር_ፖስት! እነ ዶክተር ደሳለኝ ፓርላማውን ጥለው መውጣታቸው የሚያስመሰግናቸው ነው ይህን ቀን ታ | Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

#ሼር_ፖስት! እነ ዶክተር ደሳለኝ ፓርላማውን ጥለው መውጣታቸው የሚያስመሰግናቸው ነው ይህን ቀን ታሪክ የሚመዘግበው ስለሆነ "በዛሬው የምክርቤት ውሎ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለአፈጉባኤው ያቀረቡት ጥያቄ እና ቃለምልልሱ....እንደሚከተለው ነው!

አቶ ታገሰ ጫፎ

" ... በዛሬው ዕለት የተያዙ አጀንዳዎች አንደኛ የምክር ቤቱ አንደኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ ፤ 2ኛ የፌዴራል መንግስት መስሪያ ቤቶች የ2013 በጀት ዓመት የሂሳብ፣ ፋይናንስ እና ህጋዊነት ኦዲት እና የክንዋኔ ኦዲት ሪፖርት ማዳመጥ ናቸው ፤ ...የሚቀርቡ ማስተካከያዎች እና እርማቶች ካሉ "

የአብን ተወካይ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔን " እ... "

አቶ ታገሰ ጫፎ ፤ " ቃለ ጉባኤ ላይ ነው ? "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፤ " ቃለ ጉባኤው ላይ ሳይሆን "

አቶ ታገሰ ጫፎ ፤ " አይቻልም "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፤ " አጀንዳው ላይ ቀዳሚ አጀንዳ እንዲያዝልን ለመጠየቅ ነው "

አቶ ታገሰ ጫፎ ፤ " አይቻልም ፤ ባለተያዘ አጀንዳ አንወያይም። "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፤ " የተከበሩ አፈጉባኤ ...አንድ ደቂቃ እድል እንዲሰጠኝ ጥያቄ ለማቅረብ "

አቶ ታገሰ ጫፎ ፤ " ስነስርዓት ፤ ድምፅ ማሰማት አይቻልም ስነስርዓት "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፤ " ቀዳሚ አጀንዳ እንዲያዝልን ጥያቄ ለማቅረብ ነው "

አቶ ታገሰ ጫፎ፤ " ማይክራፎኑን ይዝጉት "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ " ቀዳሚ አጀንዳ አለን የአብን ተወካዮች እሱ እድል ይሰጠን "

አቶ ታገሰ ጫፎ፤ " ማይክራፎኑን ይዝጉት፤ አጀንዳ ካለ በአማካሪ ኮሚቴ አባል ስለሆኑ በአማካሪ ኮሚቴ እንነጋገራለን "

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ " አስቸኳይ ነው ዛሬ ም/ቤቱ እንዲያይልን የምንፈልገው "

አቶ ታገሰ ጫፎ፤ " ቃለ ጉባኤ ላይ ሚቀርቡ እርማቶች እና ማስተከከያዎች ካሉ .."

ከዚህ በኃላ ዶ/ር ደሳለኝን ጨምሮ 4 አብን ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል። እነሱም፦

1.ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ (የባህርዳር ተወካይ)

2.አቶ አበባው ደሳለኝ (የጅጋ/ም/ጎጃም ተወካይ)

3.አቶ ሙሉቀን አሰፋ (ሸበል በረንታ/ዕድ ውሃ ተወካይ

4.አቶ ዘመነ ኃይሉ (የጭስ ዓባይ ተወካይ)

ለሀሳብ ለአስተያየት በዚህ ሊንክ @Tadeletibebut