Get Mystery Box with random crypto!

ሀዋን ማን ገደላት? ( አብዲ ኢኽላስ) ክፍል አስራሁለት(12) ሰሚር ከ ሆስፒታል ወቶ እቤት | S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮

ሀዋን ማን ገደላት?

( አብዲ ኢኽላስ)

ክፍል አስራሁለት(12)

ሰሚር ከ ሆስፒታል ወቶ እቤት አረፍ ብሏል።ህመሙም ቀሎታል ከአንድ ቀን በላይ እረፍት ማድረግ አይፈልግም ።ከዚህ ቡሃላ ነቃ ብሎ ወደ ስራው እንደሚመለስ እያሰበ ነው።አሁን ለሱ ውድ ልጆቹ የባለቤቱ እናት እና ተወዳጆ ባለቤቱ ሀዋ ከጎኑ ነች።ነገር ግን ይሄ የሰሚር ጭንቅላት ነው እንጂ እውነቱን ቢያውቅ ኖሮ አጠገቡ ያለችው ያቺ ከባድዋ ሙና እንጂ ሀዋ አይደለችም። ሙና በዚ ሰአት የተጣለባትን ከፍተኛ ሀላፊነት በጣም ወዳዋለች።እንደ ሀዋ ሆነሽ እራስሽን አጠንክረሽ ነገሮችን አስታውሰሽ እንደ ሚስት ሆነሽ እየተንከባከብሽው የሚፈልገውን ሁሉ እያደረግሽ ከአጠገቡ ሁኚ ተባበሪን ላላት ዶክተር ፈገግታ የተሞላበት ልዪ መልስ ሰጥታዋለች "አይዞህ ወደ ጤንነቱ ሲመለስ ሀዋን እንዲተዋት ነው ማደርገው" ዶክተሩ ግራ ቢጋባም ሙና ግን "አብሽር ሌላ ነገር እያልኩህ አይደለም ያዘዝከኝን ከልቤ ፈፅማለሁ ለማለት ነው" ብላ አሳምናዋለች።


ዶክተሩ የተመለከተው እና የሰማው ነገር አስደስቶታል የሰሚር ህመም ቢያስጨንቀውም ግራ ቢያጋባው እና አዲስ ቢሆንበትም ሙና ግን እራሷን አሳልፋ ለሰሚር እሰጣለሁ ማለቷ ከጀርባዋ ያለውን ታሪክ አያውቅም እና ደስተኛ ሆኗል እጅጉን አክብሮ አመስግኗታል።


ኻሊድ ራስ ምታት ውርር አርጎታል።ጭንቅላቱ ሊፈነዳ ምንም አልቀረውም ይህ ትንሽ ልጅ በአንድ በኩል በአባቱ መታመም ሲያለቅስ በሌላ በኩል ለቀናት በእናቱ መጥፋት ግራ ሲጋባ እና ሲጨነቅ ከዚያ ደሞ የእናቱ ገዳይ እንደሆነች የጠረጠራትን ሙናን እናቱ አርጎ እንዲቀበል ሲገደድ ብቻ ግራ ገብቶታል ።ምን ያድርግ ወደፊትም ወደኋላም ሊል አልቻለም ሙናን እንዳያጋልጥ ለአባቱ ሰግቷል እሺ ብሎ እንዳይቀበል ደግሞ በእናቱ እጅጉኑ ስጋት ወጥሮታል።ምክንያቱም እዚ ቤት ውስጥ ሀዋ እንደጠፋች ተደርጎ ነገሮች እንዲስተናገዱ መንገድ አይከፍትም አባቱ ሁኔታዎችን አምኖ ተቀብሏል።ሌላ የሚያሰጋው ነገር ደሞ ትንሿ ሱመያ ነች ሱመያ ለአንድ ቀን ተታላ ሁኔታዎችን ብትቀበልም ከቀናት ቡሀላ ግን ነገሮችን ረስታ ሚስጥር ብታወጣ እውነቱን ብትናገር ምን ሊሉ ይችላሉ? ይህ ለሁሉም ጥያቄ ነው።




እትዬ መርየም እንደሚበቃቸው ወሰኑ።አሁን ቤታቸው ሂደው የራሳቸውን ሂወት ለቀናትም ቢሆን አረፍ ብለው መኖር እንዳለባቸው ለራሳቸው ነገሩ።ምክንያቱ ደሞ ሀዋ እንደተመለሰች የሚያስበው ሰሚር ነገሮች እንደሞሉለት አርጎ ሙሉ ሰው ለመሆን ስለተነሳ ነው።በዚ ሂደት ውስጥ አጋዥ ደጋፊ ተባባሪ እና አስታማሚ ቦታ የለውም ሁሉም ጤነኛ ሁሉም ሙሉ እንደሆነ ነገሮች ተመሳስለው ተቀይጠዋልና።



በዚ ሁኔታ ላይ ሳሉ የግቢው በር ተንኳኳ።እንደሁልጊዜው ኻሊድ ሮጦ ከፈተ።ኻሊድ በሩን ሲከፍተው ሲጠብቀው የነበረው ነገር የማይቀርለት ሂደት ቀኑን ጠብቆ መጣ።ኢኒስፔክተር ግርማ ከተፍ አለ ዛሬ እንጀመቼለታው እንደማይሸውደው እቤት የሉም ብሎ እንደማያታልለው እርግጠኛ ሆኗል።ምክንያቱም ይሄን ያህል ቀናት ከቤት ጠፍተው የትም እንደማይሄዱ እርግጠኛ ሚሆነው ፖሊስ እዚ ቤት ከሌሉ ያሉበትን አድራሻ ጠቁመኝ እንደሚለው ኻሊድ በእጅጉን ተረድቷል።ስለዚህ ያለው አማራጭ ወደቤት ማስገባት ነው።በትንሽም ቢሆን እድል ሚሰጣቸው የሰሚር እንቅልፍ ላይ መሆን እና መኝታ ቤት ውስጥ መቀመጥ ነው።ሰሚር ድምፅ ማይሰማበትን ሁኔታ ማመቻቸት ከቻሉ ኢኒስፔክተሩ ቢገባም እንኳ ምንም ችግር ሳይፈጠር ሊወጣ እንደሚችል አምነዋል።ስለዚህ ኻሊድ ምንም እንኳን የማሰቢያ ጊዜ ባያገኝም ኢኒስፔክተሩን ወደውስጥ እንዲገባ በር ከፈተለት አብረው ገቡ። ከዚያም ከሳሎን እንዲቀመጥ ካደረገው ቡሀላም ኻሊድ ወደ ሙና ሮጦ እንዲህ አላት"አሁን ፖሊሱ መቷል ስለዚ አንቺ ቶሎ ብለሽ ሰሚር ጋ ግቢና እንዳይነቃ አርጊው ከእንቅልፉ ከነቃ እንኳን ወደ ሳሎን እንዳይመጣ ከዛም አልፎ ሳሎን ውስጥ የምናወራውን ነገር እንዳይሰማ ለማረግ ሞክሪ እንደዛ ካልሆነ እኮ ፖሊሱ ገብቶ ይረብሻል።አንቺ ደሞ ሀዋ አይደለሽም ስለዚህ ሰሚር ሀዋ ብሎ ሲጣራ እንኳን ፖሊሱ ቢሰማ ነገሩ አንቺ ላይ ይከርብሻል!"ብሎ አሳመናት።ሙና ኻሊድ ያለው ነገር መቶ በመቶ አስማምቷቷል በደስታ ወደ ሰሚር ክፍል ገብታ በሩን ከውስጥ ቆለፈች ከዚያም ኢኒስፔክተሩ ጋር እትዬ መርየም እና ኻሊድ ቀረቡ።ነገር ግን የሙና ወደ ውስጥ መግባት ለ ኢኒስፔክተሩ ሰላም አልሰጠውም።እሷንም ማናገር እንደሚፈልግ ነገራቸው ይሄኔ የኻሊድ እቅድ ከሸፈ ሙና እንድትጠራለት ያዘዘው ፖሊስ ሀሳቡን ተቀብለው ሙናን ከሰሚር ተለይታ ወደ ሳሎን መታ አብረው በጠረጴዛ ዙርያ ማውራት ጀመሩ።ነገር ግን የኻሊድ እና የሙና ደጋግሞ ወደ መኝታ ቤት መመልከት አሁንም ለ ኢኒስፔክተሩ ሰላም አልሰጠውም በውስጥ አንዳች የተደበቀ ነገር ለመኖሩ ጥርጣሬ እንዲያመጣ በር መክፈቱን ጀመረ።ይሄን የተረዱት ሙና እና ኻሊድ ፊታቸውን ወደነበረበት መልሰው ማስመሰሉን ተያያዙት።ከዚያም ኢኒስፔክተር ግርማ ጥያቄዎቹን ጀመረ እነሱም መመለሱን ቀጠሉት የዛን ቀን ምሽት ምን ተፈጠረ ስንት ሰአት ነበረ ከዛ ምን ሆነ እንዴት ነበረች ከማን ጋር አውርታ ነበረ የግርማ ጥያቄዎች ናቸው።እነሱም መልሱን የሚያውቀው ሁሉ ጣልቃ እየገባ መመለስ ጀመረ ።ኢኒስፔክተሩ ከመሀከላቸው ወንጀለኛ ነው ብሎ የሚጠረጥረው አንዳችም ሰው የለምና እንዲያው ቃላቸውን ብቻ ፈልጎ ጥያቄዎች ሲያዥጎደጉድ ስለነበረ የሚፈልገውን ጥያቄ እየተባበሩ መለሱለት።ይሄኔ በቀጣይ ቀን መቶ ተጨማሪ ምርመራ እንደሚያደርግ ለምስክርነት እና ቃል ለመስጠት ሲፈለጉ እንዲገኙለት ነግሯቸዋል ለመሄድ ብድግ አለ።ለመውጣት በመሰናዳት ላይ ሳለ የሰሚር ክፍል ውስጥ ተቀምጦ የነበረው የሀዋ ስልክ ድንገት ጮኸ።ይሄኔ ሰሚር ከእንቅልፉ ባነነ መኝታ ቤት ውስጥ እንዳለም ድምፅ ማሰማት ጀመረ። "ሀዋ ሀዋ ስልክ ሀዋ "አለ ሰሚር ኢኒስፔክተር ግርማ ይሄን ድምፅ ሲሰማ በድንጋጤ እና ግራ በመጋባት አንዳች ነገር እንዳገኘ ተሰምቶት ወደ ሰሚር ክፍል በፍጥነት አመራ።


ክፍል አስራ ሶስት(13) ይቀጥላል........


#ልዩ_ምስጋና: ለሰኪና ራህመቶ

@Strong_iman