2022-07-07 09:29:44
#ነጥብ_ሁለት
#ኢኽዋህ(إِخْوَة)
የሙሳ ወንድም እና የመርየም ወንድም አንድ ማንነት ናቸው ስንል አማኞች ወንድም እና እህት ናቸው በሚል ቀመርና ስሌት ነው ይሉናል። ይሄም የሙግት ነጥባቸው መፍለክለኪያ(ማምለጫ) ያጣ ሰው ለማምለጫ ከሚፈጥረው ቀዳዳ ተለይቶ አልታየኝ። በሃገሬው አባባል "...ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ..." እንደሚባለው ነጥቦቻቸው የመሐመድን ስህተት መደበቅ ሳይችልላቸው ሲቀር ከአንዱ ወደ አንዱ በይሻላል መንፈስ ይራወጣሉ። ለማንኛውም በአማኞች መካከል ኢኽዋህ(إِخْوَة) ማለትም ወንድማማችነትና እህትማማችነት ቢኖርም አሁንም የሱረቱል መርየም(19:28) ከጥያቄ አያመልጥም።
ቁርአኑ ስለ ሙሳ ከወንድሙ ሃሩን ይልቅ በስፋት ነግሮን ሳለ ሙሳ ሳይጠቀስ ሃሩን የተጠቀሰበት አግባብ ግልጽ አይደለም።
ደግሞስ መርየም አባቷ ኢምራን እያለ በሙሳ ወንድም በሃሩን ስም መጠራቷ ምንን ያመለክታል? ደግሞም በሌላ ክፍል በሱራ 33 እና 66:12 ላይ “የኢምራን ሴት ልጅ” በመባሏ ወደ ሱራ 19:28 ስንመጣ ከሩቅ ዘመን ባለ ሰው ስም መጠራቷ ጉዳዩን የበለጠ ብዥታንና እና ችግርን አስከትሏል። ለዚህ ሁሉ ጥያቄ መልስ የሚሆነው የመሐመድን ስህተት መቀበል ነው።
በተጨማሪም መሐመድን ለዚህ ትልቅ ስህተት ያበቃው አንዳንድ ምንጫቸው በቅጡ ከማይታወቁ በክርስትናው ላይና በአይሁዳውያን መጽሐፍት ላይ ከሚጨመሩ አፈታሪኮች የሰማውን በራሱ አገላለጽ ስለሚዘግብ ነው።
ሱረቱ-መርየም የተወሰኑ ክፍሎች
የአፖክሪፋን ታሪኮች እንደ የያዕቆብ ፕሮቶቫንጄሊየም (Protoevangelium of James) እና የሐሰተኛው-ማቴዎስ ወንጌል(gospel of Pseudo-Matthew) ካሉ አፈ ታሪኮች የአዋልድ ታሪኮች ተመሳሳይነት ያለው ታሪክ እናገኝበታለን። ለምሳሌ የቴምር ዛፉ ስር የተፈጠረው ታሪክ[⁵] ስለ መርየም ወላጆች ታሪክ[⁶] ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም በአረባዊቷ ምድር በፍልስጤም ውስጥ በቅድስት ድንግል ማርያም የተሰየመ የባይዛንታይን ቤተክርስቲያን አለ። ይህ ቤተክርስቲያን ከእስልምና ወግ ጋር ጥልቅ እና የተወሳሰበ ግንኙነት አለው እንዳለው ታሪክ ይነግረናል። በመሐመድ ዘመን አካባቢ ይህች ቤተክርስቲያን የክርስትና አምልኮ ማዕከል ነበረች። በቅዳሴ ወቅት ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ከሚነበበው ከካቶሊክ እና ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተቃራኒ በዚህ ጊዜ ለንባብ ከአፖክሪፋ እና ከሌሎች ቀኖናዊ ያልሆኑ መጽሐፍት መነበቡ የተለመደ ነው። በተጨማሪም የተለያዩ የክብረ በዓላት የምታከብር ቤተ ክርስቲያን ነበረች። ለምሳሌ ላይ በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ቀን 14 ከነብዩ ኤርምያስ ሕይወትም ከአዋልድ መጽሐፍት ይነበብ ነበር። በምንባቡ ላይ መሐመድ በሱረቱል በመርየም ላይ እንዳሰፈረው አይነት ማለትም ሃሩን(አሮን) የማርያም (መርየም) ወንድም በማለት የተጠቀሰን ጽሑፍ እናገኛለን[⁷]፦
“ነቢዩ [ኤርምያስም] እንዲህ አለ - መምጣቱ ለእርስዎ እና ለሌሎች ልጆች በዓለም ምልክት መጨረሻ ይሆናል ።
57 እንዲሁም የተደበቀውን ታቦት ከዓለት ላይ የሚያወጣ የለም #ከማርያም #ወንድም_አሮን በስተቀር ።
(The Lection of Jeremiah)
በተመሳሳይ ሁኔታ ቁርአኑ ስለ ማርያም (መርየም) ሲናገር ሃሩን(አሮን) የማርያም (መርየም) ወንድም እንደሆነ ዘግቦልን አግኝተናል፦
19፥28 « #የሃሩን_እኅት_ሆይ! አባትሽ መጥፎ ሰው አልነበረም፡፡ እናትሽም አመንዝራ አልነበረችም» አሏት፡፡ يَا أُخْتَ هَارُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ امْرَأَ سَوْءٍ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّا
በመጨረሻም ለመሐመድ ዘብ እንቆማለን ባዮቹ አብዱሎች ታሪክን በመደበቅ የመሐመድን ስህተቶችና አላዋቂነቱን ለመደበቅ መፍጨርጨራቸው የሚያዋጣ አይደለም። መሐመድ ከታሪክ አንጻር ሲሳሳት ይሄ የመጀመሪያው እንዳልሆነ ከታሪክ መዛግብት ዘንድ ብዙ መረጃዎችን ስንበረብር የሚጋለጥ ሐቅ ነው። በሚቀጥለው በሌላ የመሐመድ የታሪክ ስህተትን እየጠቀስንና እያጣቀስን(ከአብዱሎች አባባል የተወሰደ) እስከምንገናኝ በክርስቶስ ፍቅር ቸር ሰንብቱ!!!
Jonathan(Yeshua Apologetics)
ማጣቀሻዎች እና ማስፈንጠሪያዎች
[¹] https://al-maktaba.org/book/9783/383
[²] የተለያዩ የታሪክ ተመራማሪዎች እና ጸሐፊዎች ስለ ሙሴ የውልደት ዘመን ላይ የተለያየ አስተያየቶችን ሰንዝረዋል። በአማካይ ከወሰድነው ሙሴ እና ወንድሙ አሮን የተወለዱት 1400-1500 ዓ.ዓ ገደማ እንደሆነ አብዛኞቹ ምሁራን ይስማሙበታል(Seder Olam Rabbah,
Jerome's Chronicon (4th century) gives 1592 for the birth of Moses,The 17th-century Ussher chronologycalculates 1571 BC (Annals of the World, 1658 paragraph 164)
[³] The gospel of the birth of Mary, 1:1-2, Gambero, Luigi (1999). Mary and the Fathers of the Church: The Blessed Virgin Mary in Patristic Thought. Ignatius Press.ISBN 978-0-89870-686-4.
[⁴] http://quran.al-islam.com/Page.aspx?pageid=221&BookID=11&Page=1
[⁵] The Gospel of Pseudo-Matthew Chapter 20
[⁶] Protoevangelium of James Gospel
[⁷] Guillaume Dye, “The Qur’ān and its Hypertextuality in Light of Redaction Criticism,” The Fourth Nangeroni Meeting Early Islam: The Sectarian Milieu of Late Antiquity? (Early Islamic Studies Seminar, Milan) (15-19 June 2015)
104 views06:29