Get Mystery Box with random crypto!

SEBIL TUBE

የቴሌግራም ቻናል አርማ sebil_tube — SEBIL TUBE S
የቴሌግራም ቻናል አርማ sebil_tube — SEBIL TUBE
የሰርጥ አድራሻ: @sebil_tube
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.31K
የሰርጥ መግለጫ

قُل هذِهِ سَبيلي أَدعو إِلَى اللَّهِ عَلى بَصيرَةٍ أَنا وَمَنِ اتَّبَعَني وَسُبحانَ اللَّهِ وَما أَنا مِنَ المُشرِكينَ ﴿١٠٨﴾
"ይህች መንገዴ ናት። ወደ አላህ እጠራለሁ። እኔም የተከተለኝም ሰው በግልጽ ማስረጃ ላይ ነን።ጥራትም ለአላህ ይገባው። እኔም ከአጋሪዎች አይደለሁም"በል።
ቁር 12:108
@minhu99
@Mahiro_k

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-10-06 22:40:40
ከሰሃቦች መካከል የነበረው ረቢዓ ኢብኑ ከዓብ አል አስለሚ (ረ.ዓ) ከውዱ መልዕክተኛ ﷺ ጋር ረፋድ ላይ መቀማመጥን ያዘወትር ነበር፥ ከሳቸው ጋር ብዙ ጊዜ ማሳለፍን እጅግ የሚወድ ፥ ውዱዕ የሚያደርጉበትንም ውሃ ያመጣላቸው ነበር።

ከዛም አንድ ቀን ረሱል ﷺ ድንገት " ረቢዓ ሆይ! ምንድነው የምትፈልገው? " አሉት

ረቢዓ ምንም ሳያቅማማ... ቆይ ላስብበት ሳይል
"አስዐሉከ ሙራፈተከ ፊል ጀና : በጀነት የእርሶን ጉርብትናን እጠይቃለው " አላቸው... 'ሌላ የምትፈልገው የለህም?' አሉት 'የለኝም..ጥያቄዬ እሱ ብቻ ነው' ነበር መልሱ።

" እንግዲያውስ ይህንን ፍላጎትህን(ጥያቄህን) ለማሳካት ሱጁድህን አብዛ " አሉት ነብዩ ﷺ

ያ ረብ! የረሱልን ﷺ ጉርብትና ወፍቀን!

የአላህ ሰላት እና ሰላም በከውኑ ጀምበር ﷺ ላይ ይስፈን

@sebil_tube
@sebil_tube
202 viewsSadelvat , 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 22:27:26 ለጋ የወጣትነት ጊዜውን ለኢስላም ሲል የሰዋ፤ እንደሻማ ቀልጦ የበራን ጀግና ልንዘክር የሻም ምድርን ረገጥን። የጀግንነት ገድሉን ከመተረካችን በፊት ወደ ኋላ እንመለስ። የሻምን ከተማ ለደቂዎች ለቀን ወደኪናናዋ ሚስር በሐሳብ እንክነፍ።
ዘመኑ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1798 ዓመት ነው። የእስክንድርያ የባህር ዳርቻዎች በናፖሊዮ በሚመራ ጦር ተጨናንቋል። በቡድን ቡድን ተጭነው ወደ ግብፅ እየገሰገሱ ነው፡፡ ይህ ዘመቻ “ግብፅን በክርስትና የማቅናት ዘመቻ” የሚል መጠርያ ስያሜ ተሰጥቶታል።
ኑ ተከተሉኝ አረመኔያዊ ግፋቸውን እናውሳ! በግብፅ ሙስሊሞች ላይ ያደረሱትን ጥፋት እንዘክር! መሳጂዶችን ምን እንዳደጉ እንተርክ!

ናፖሊዮ በአውሮፓ ውስጥ አብያተ ክርስቲያናትን ማፍረሱን፣ የአላህ መልዕክተኛን እንደሚወድና በእስልምና በእጅጉ መማረኩን ለአል-አዝሃር መሻኢኾችና ታዋቂ ሰዎች በወረቀት ላይ አስፍሮ ሰደደ፡፡ ወደ ግብፅ ከመምጣቱ በፊት የሮማውን ሊቃነ ጳጳሳት ከሥልጣን እንዳወረደ ጠቅሶ ፃፈ። ነገር ግን ይህ የቆየ ብልሃት የግብፅን ህዝብ አልሸወደውም። “የመጀመሪያው የካይሮ አብዮት” ብልጭታ በፈረንሳዮች ላይ ተቀጣጠለ። የባህል እና የሥልጣኔ ተሟጋቾች ነን የሚሉት ፈረንሳዮች ማንነታቸው ተጋለጠ። በልባቸው ውስጥ ያጨቁትን የመስቀለኝነት መንፈስ ከጦራቸው ጋር ሸክፈው አዝሃርን በመውረር የአላህን ቃል ቁርአንን በእግራቸው ረገጡ። “በሞቅታም ተራራ” ላይ መድፎችን አዘጋጁ። የግብፅን ሰፈሮች አፈረሱ። “ቡላቅ” የተባለውን መንደር ወደ ፍርስራሽነት ቀየሩ። የአላህ ቤት መሳጂዶች ወደሙ፡፡ በአንድ ቀን ውስጥ የፈረንሳይ የመስቀል ጦር ሁለት ሺህ የአል-አዝሃር ምሁራንና መሻኢኾችን ገደለ። ዱዓቶችን አረደ። ሙስሊሞች ከቀድሞዎቹ የተለየ ያልሆነ የመስቀል ጦርነት እየገጠማቸው መሆኑን ተገነዘቡ፡፡ በዚህ ጊዜ የአል-አዝሃር ደረሶች በአላህ መንገድ ለመፋለም ተነሱ።

ግብፃዊው የታሪክ ምሁር ፀሐፊ አል-ጀበርቲ “عجائب الآثار في التراجم والأخبار” በተሰኘው መጽሐፉ ላይ የመስቀል ጦር ትብብር እንዴት እንደነበረ ይናገራል። ከዳተኛው ሙ#ናፊ#ቅ "ያዕቁብ ሐና" የአገሬው ሰዎችን አስጨፈጨፈ። ጠንካራ ሙስሊሞች ላይ እየጠቆመ ወደ ቤታቸው ዘልቀው በመግባት ለፈረንሳዮች እየጠቆመ ሙስሊም ወንድሞቹን አስገደለ።
ናፖሊዮን የግብፅን አመፅ መቅበሩን ሲያረጋግጥ መሪነቱን ለሌላ የጦር ወንጀለኛ (ክሊፕተር) አስረክቦ የመስቀል ተልዕኮው መጠናቀቁን ለማበሰር ወደ ፈረንሳይ ተመለሰ።

ይህ የመስቀላዊያን ጦር መሪ ሥነ ምግባር የጎደለው የሙስሊሞች ጥላቻ የተጠናወተው ነበርና የስልጣን ልጓሙን እንደተቆጣጠረ ከውድመት የተረፉትን መሳጂዶች የመስቀል ወታደሮችን ለማዝናናት ወደ ጭፈራ ቤትነት ቀየራቸው። ሙስሊም ልጃገረዶችን በአባቶቻቸው ፊት መስጂዱ ውስጥ ደፈሯቸው። ሕፃናትን በእናቶቻቸው ፊት ገደሉ። ከተማዋ ሰሚ ባጣ የዋይታና የኡኡታ ጩኸት ተሞላች። እስልምና ግብፅ ውስጥ አከተመ ተባለ . . .

ሙጃሂዶች በመላ ግብፅ “የላኢላሀ ኢለላህን" ሰንደቅ ዓላማ በማንሳት ከሁሉም አቅጣጫ ተነሱ። በመስቀል ጦር ላይ ጥቃትን ሰነዘሩ። ከመካ እና ከመዲና አጋዥ ኃይሎች መጡ። የሂጃዝ ሙጃሂዶች ለሙስሊም ወንድሞቻቸው ድጋፍ ለመስጠት ወደ ግብፅ የባህር ዳርቻ በመርከብ ተጭነው ተመሙ። በሺዎች የሚቆጠሩ የቱርክ ተዋጊዎች በድብቅ ሰርገው ገቡ። ኦቶማን ኢምፓየር (በደውለተል ዑስማኒያ) መሪ ሰሊም በታወጀው ጂሃድ ለመካፈል ከየአቅጣጫው ሙስሊሞች ወደ ካይሮ ገሰገሱ። አል-አዝሃርም ወደ ካምፕነት ተቀየረ።
የፈረንሣይ መስቀለኞች መስጂዶችን በፈረሶቻቸው እየረጋገጡ ሲያረክሱ የተመለከተው የዛሬው ባለታሪካችን የሀያ ሁለት ዓመቱ ወጣት፣ የኩርዱ ጀግና ነፍሱን መስዋእት የሚያደርግ ቢሆን እንኳ እነዚህ ነፍሰ በላ የመስቀል ጦረኞችን ለማዋረድ ብሎም ለመበቀል ስኬታማ የሆነ ኦፕሬሽንን ለማከናወን አሰበ። ሱለይማን አል-ሀላቢ ይሰኛል። ብቻውን ወደ ፈረንሣይ ካምፕ ዘልቆ በመግባት የጦር አዛዡን ለማጥቃት ወሰነ፡፡ ይህንን ተግባር ለማከናወን እቅድ ነደፈ። አሳቻ ሰዓትም ይጠባበቅ ጀመር። ወቅቱ ደረሰ በመስቀል ጦር ወራሪ ኃይሎች ላይ የተሳካ እርምጃን ወሰደ። የመስቀለኞችን ጦር መሪ በመግደል ፈረንሳዮችን አስደነገጠ። ሙስሊሞችን ከጥቃት ታደገ። ተማረከ! አዎ ተማረከ! እጃቸው ላይ ወደቀ። ግና ሱለይማን አል-ሀላቢን ምን እንዳደረጉት ጆሯችሁን ቀስራችሁ አድምጡኝ ትማሩበት ዘንድም ቀልባችሁ ከፍታችሁ ስሙኝ።

እጁን አጥንቱ እስኪታይ ድረስ በእሳት አቃጠሉት። ከሱ ጋር ተባብረዋል ያሏቸውን ሶስት በፍልስጤም “ጋዛ” ነዋሪ የሆኑ ልጆችን አይኑ እያየ ፊትለፊቱ አቃጠሏቸው፡፡ የዘመናዊነት እና የሥልጣኔ ተሟጋቾች ሱለይማን አል-ሀላቢን ሹላማ ብረት አግለው በጀርባው በኩል እያስገቡ አንጀቱን ቀጥሎም ኩላሊቱን እየጎለጎሉ አወጡት። ሹሉን ብረት በመቀመጫው በኩል እየሰቀሰቁ አሰቃዩት። የብልቱን ፍሬ ቆርጠው ገደሉት። አዎ ገድለው ለብዙ ቀናት ዛፍ ላይ አንጠለጠሉት በወፍና አሞራዎች እንዲበላ አደረጉ፡፡
በዚህም አልረኩም የራስ ቅሉን ወስደው ፓሪስ “musee de ihomme” በሚገኘው ሙዚየም ውስጥ አስቀመጡት ከበድኑ ስርም በፈረንሳይኛ "criminel" በሚል ፅሑፍን አሰፈሩ "ወንጀለኛ" እንደማለት ነው። የዚህ ሙጃሂድ የራስ ቅል በሙዝየማቸው ውስጥ እስከ አሁን ድረስ ይገኛል። ፈረንሳዮች እንደሚሉት ወንጀለኛ አልነበረም። እሱ ለኢስላም ሲሉ ካበሩ ምርጥ የኢስላም ወጣት ጀግኖች መካከል አንዱ ነበር። ወጣትነቱን እንደ አበባ የፈካ እድሜውን በአላህ መንገድ የሰዋ ድንቅ ሰው፡፡ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የአላህን ቃል እየቀደዱ የፈጸሙትን ግፍ በመበቀል ገሎ በክብር የሞተ። ለበደላቸው እና ለጭካኔያቸው ተስማሚ የሆነ የበቀል እርምጃ የወሰደ ወጣት።
አላህ ይቀበለው

═════════════════
ምንጭ
عجائب الآثار في التراجم والأخبار

@sebil_tube
@sebil_tube
═════════════════
205 viewsSadelvat , 19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 14:48:13
ሱለይማን አልሀላቢ ማነው?

@sebil_tube
@sebil_tube
246 viewsSadelvat , 11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 13:05:49 በአላህ ስም እጅግ መጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው! የአላህ ሰላም እዝነትና በረከት በውዱ ነቢያችን ላይ ይሁን!


#አቂሚ_ሶላት

የሶላት ጩሩጦች (ሕጎች)

#ክፍል12

#የሶላት_ግዚያት


وقت الظهر: من زوال شمس إلى أن يسير ظل كل شيء مثله زاءدا على فى أزوال.
ٱذا طلعت الشمس ونصبت شيءا شاكصا كالعصا أو غيره صار له ظل. هذا ألظل كلما إرتفعت الشمس نقص حتى يقف. فإذا إنتهى وبدأ يزيد فحينءذ زالت الشمس، إجعل علامت من بدء زيادته، فإذا إمتد الظل من هاذه العلامه إلى رأسه بمقدار الشاكص فقد خرج وقت ظهر، ودخل وقت العصر.


የዙህር ሶላት ወቅት(ግዜ)

DEFINITION =ማብራሪያ፦

የዙህር ሶላት ወቅት ፀሐይ ማሀከል ደርሳ ከመኸከል ዞር ካለች ጀምሮ የሁሉም ነገር ጥላ ቁመት ከነገሩ ጋር ኡኩል እስኪሆን ድረስ ነው።


EXPERIMENT= ሙከራ፦

ለምሳሌ ፀሐይ ስቶጣ የሆነ ነገር እንጨት እንደ ችካል ብትተክሉ ወይም ከዛ ውጪ ያ የተከላቹት ነገር ጥላ ይኖረዋል። የዚህ የተከላቹት ነገር ጥላ ፀሓይ ወጥታ ከፍእያለች ወይም ወደ ማሃል እየተጠጋች በመጣች ቁጥር የተከላቹት ነገር ጥላ ይቀንሳል ፀሓይ መሃል እስክትደርስ ድረስ። ፀሐይ መሃል ከደረሰች አሁንም መሄድ ትጀምራለች ያኔ #የዙህር_ሶላት ገብቷል። ባጠቃላይ የዙህር ሶላት ወቅት ፀሐይ ከመሃል ዞር እንዳለች ገብቷል ማለት ነው። አሁን ያ የተከላቹት ነገር ጥላ እንደ አዲስ መጨመር ይጀምራል። ይሄ ጥላ ጨምሮ ከተከላቹት ነገር ወይም እንጨት ጋር እኩል ሲሆን #የዙህር_ሶላት ወቅት ያልቃል። #የአስር_ሶላት ወቅት ይገባል ማለት ነው።


ወንድም ያሲን

ያልገባቹ ነገር ካለ መጠየቅ ትችላላችሁ!
ለአላህ ብለን እንወዳችኋለን!



@sebil_tube
@sebil_tube
@sebil_tube
1.5K viewsYasin Huseen, 10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 07:46:01 Rabbiin Mindaa Gabroota isaa gaggaarii qopheesse akkanatti ibsa:

فَلَا تَعْلَمُ نَفْسٌ مَّا أُخْفِيَ لَهُم مِّن قُرَّةِ أَعْيُنٍ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ (17)

"Wanta isaan hojjataa turaniif mindaa akka ta’uuf gammachuu ijaa irraa wanta isaaniif dhokfame lubbuun tokkoyyuu hin beektu.” Suuratu As-Sajdah 32:17

Aayah tana ilaalchisee Rasuulli (sallallahu aleyh wassallam) akkana jedhan, “Rabbiin olta’aan ni jedha, “Gabroota Kiyya gaggaariif wanta ijji hin agarre, gurri hin dhageenye fi qalbii namaa irra hin qaxxaamurre qopheessefi jira.”  Sahiih Al-Bukhaari 4780

SHARE
@sebil_tube
SHARE
@sebil_tube
315 viewsIMRAN ORO, edited  04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:46:48
ለቸርች ተብሎ ህዝብ ያጠራቀመውን ገንዘብ በመውሰድ ለሚስቱ ቅንጡ መኪና የገዛው ናይጄርያዊ ፓስተር ፊቱን አበጥረው የተነፋፋ ጎማ አድረግውታል

የኛዎቹስ ተራ መች ይሆን ??

@sebil_tube
@sebil_tube
273 viewsSadelvat , 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:25:07
ዑመር ሙኽታር ባለቤታቸው ይህቺን ምድር ለቃ ወደ ቀብር በተጓዘች ጊዜ በእጅጉ አምርረው አለቀሱ። የጦር ባልደረቦቻቸውም ለምን እንዲህ ተንሰቅስቀው ያነባሉ? በማለት ጠየቋቸው
ዑመር ሙኽታር "ጣልያውያንን ከተዋጋሁ በኋላ ወደ ቤት በገባሁ ቁጥር የድንኳኑን በር ከፍ አድርጋ ታስገባኝ ነበር። ለምን እንደዚህ እንደምታደርግም ስጠይቃት ሳታቀረቅር አናትህን ሁሌ ከፍ እንድታደርግ እፈልጋለሁ ለምንም ነገር እንድትጎነበስ አልሻም ትለኝ ነበር" ሲሉ መለሱ።

@sebil_tube
@sebil_tube
270 viewsSadelvat , 18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:23:40 "እኛ ሃገር ሳይሆን ልቦችን ልንከፍት ነው የመጣነው" ሙሐመድ አል ፋቲህ ቆስጠንጢኒያን በድል የከፈተ ቀን የተናገረው

@sebil_tube
@sebil_tube
245 viewsSadelvat , 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:22:06 አቡበከር አልሚስኪ ይሰኛል። ሰውነቱ በሚያመነጨው መልካም ሽታ ምክንያት ሚስኪ የሚለው ስያሜ ተችሮታል።
"ሁሌም ከአንተ የሚስክን ጠረን እናሸታለን ምክንያቱ ምን ይሆን?" ሲሉ ጓደኞቹ በአንድ ወቅት ጠየቁት።
"በአላህ ይሁንብኝ ለብዙ አመታት ምንም ዓይነት ሽቶ ሰውነቴን ሳይነካኝ ቆይቷል" አለና ለደቂቃዎች በዝምታ ተዋጠ። ንግግሩን ቀጠለ "ከእለታት በአንዱ ቀን አንዲት ሴት ወደ ቤቷ ጠራችኝ። ከገባው በኋላ በሩን ቆለፈችብኝ። ከርሷ ጋር ዝሙት እንድፈፅም ያ ካልሆነ ሊደፍረኝ ሞከረ ብላ እንደምታሲዘኝ ዛተችብኝ። ግራ ተጋባሁ። የጌታዬን ሀቅ ለመጠበቅ የእርሱን ክልከላ ላለመዳፈር የገባሁትን ቃል ላለማፍረስ ተጋሁ። ብለምናት አላህን እንድትፈራ ብማፀናት አሻፈረኝ ብላ በአቋሟ ፀናች። ወደመፀዳጃ መሄድ እፈልጋለሁ ስወጣ የፈለግሽውን እናደርጋለን አልኳት።

ሀማም ገባሁ። አይነምድሩን በእጄ እየዛቅኩ ሰውነቴን መቀባት ጀመርኩ። ከአናት ፀጉሬ እስከ እግር ጥፍሬ ተለቅልቄ ከሽንት ቤት በመውጣት ወደእሷ ተመለስኩ። ቤቱን አገማሁት በዚያ ሁኔታ ላይ ሆኜ ባየችኝ ጊዜ በጣም ተደነቀች። አፍንጫዋን ይዛ እንድወጣም አዘዘችኝ። ወደቤት ተመልሼ ገላዬን ታጠብኩ።
በነጋታው ለሊት ህልም አየሁ፡- “ማንም ያላደረገውን አድርገሀል። ጠረንህ በዱንያም በአኺራም ጣፋጭ ይሆናል” የሚል ጥሪን ሰማሁ። የሚስክ ሽታ ሸተተኝ ይሄው እስከ አሁን ይህ ሽታ ከሰውነቴ። እየመነጨ ሰዎችን ማወዱን ቀጥሏል”

ምንጭ:-

موسوعة الأخلاق والزهد والرقائق ١/‏٢٨١
#موعظة_لكل_المسلمين

@sebil_tube
@sebil_tube
259 viewsSadelvat , 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ