የበለዓም ትምህርት
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
(ዘኁልቁ24&25)(2ጴጥ2:15) (ይሁዳ1:11)(ራዕ2:14)
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ጠላት ሰይጣን ሁሌ እኛን የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ እንደሚዞር የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል ሁሌ የሚዞርበት ምክንያቱ ተስፋ አለመቁረጡ ነው ሁሌም እኛን ለማጥቃት ይሞክራል አባታችን እግዚአብሔር ግን ስለሚጠብቀን በሰላም እንኖራለን ጠላት ሁሌ ይረግመናል፣ ያስፈራራናል፣ ክፉ ነገር ይመኝብናል አሁንም ግን እኛ #ምንም #አንሆንም አንድ ነገር እስከምናደርግ ድረስ በዛ ነገር ከተገኘንለት ግን መረቡ ውስጥ እንገባለን ይሔም ጉዳይ የበለአም ትምህርት ነው በብሉይ ዘመን አንድ ባላቅ የሚባል ንጉሥ በለዓም የሚባልን 'ነቢይ' አስጠርቶ የያዕቆብን ልጆች አይሁድን ሊያስረግም ሞከረ ነገር ግን አልሆነም እግዚአብሔር የተባረከ ህዝብ ነው አትርገመው አለው (እኛም በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍረራ በመንፈሳዊ በረከት መባረካችንን አስታውሱ) እናም በለአም ሊረግም ሲል ግን ከአንደበቱ ባርኮት ነበር የሚወጣው በሗላ ላይ ግን የእስራኤላውያንን ደካማ ጎን ስላወቀ አንድ ክፉ ምክር በመስጠቱ ብዙ እሰስራኤላውያን ሊቀሰፉ ችለዋል እርሱም ያደረገው ሕዝቡ ከሌላ ህዝብ ጋር በማመንዘር እንዲረክስና ህዝቡ ቅድስናውን እንዲያጣ ነበር እንዳለውም ብዙ እስራኤላውያን ከእግዚአብሔር መንገድ ዞር በማለታቸው ጠፉ እኛም ከዚህ የምንማረው ሰይጣን ቅድስናችንን በማጉደፍ እግዚአብሔር ከሰራልን ብርቱ ቅጥር በአመጻ እንድንወጣ እና ለጥፋት እንድንጋለጥ ያደርገናል ስለዚህ ጌታ በሚሰጠን ጸጋ ከጌታ ፍቃድ ከሚያወጡን ለስጋ ከመመቹ አጥፊ ከሆኑ የዘመናችን በለዓም ትምህርቶች መጠበቅ ነው (መክብብ10:8) ላይ ቅጥርን የሚያፈርስ እባብ ትነድፈዋለች ይላል ስለዚህ የቅድስና ቅጥር መፍረስ የለበትም ማለት ነው መጠንቀቅ ያለብን የጠላትን እርግማን ሳይሆን ወደ ልብ የሚገባና የሚመርዘውን የጠላትን ክፉ ትምህርት ነው።
#ጸሎት
እግዚአብሔር ሆይ ስለ ቃልህ በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ተባረክ አባት ሆይ ሕይወታችንን ከሚያበላሽ ከቅድስና እንድንጎድል ከሚያደርግ ከበለዓም ምክር ልባችንን ጠብቅ ጌታ ሆይ በልባችን ያለ ማንኛውም ክፉ አሳብ በልጅህ ደም አስወግድልን የጠላትን ሀሳብ እንዳንስት ልባችንን በማስልዋል ሙላ ጸጋህ ከአለማዊ ምኞት ይጠብቀን አብ አባት ሆይ በአለም ምድረበዳ በመንፈስህ ምራን እጃችንን ይዘህ ምራን ስለሰማኸን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተባረክ! ክብር ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ይሁን አሜን፡፡
#join and#share #share