" እጅ_ከፍንጅ " - አንዲት ባለትዳር ፥ በጓዳዋ ሳለች ፥ ጉንዳን ቆነጠጣት ከእግር እስከ ራሷ ፥ ተርመስምሶ ገብቶ ፥ ነክሶ ፋታ አሳጣት - ይሄን ጊዜ ጮኸች፤ ልብሶቿን አራግፋ ፥ ራቁቷን ቀረች! - ጩኸቷን የሰማ ፥ ላጤ ጎረቤቷ ፥ ገባ ተንደርድሮ ያቺን ቆንጆ እንስት ፥ እርቃኗን ሲያያት ፥ ቀረ ተገትሮ! - በዚህ ሁነት መሃል ፥ ሰይጣን አይኑን ሲጥል ፥ ባል ድንገት ይደርሳል ሰበብ የጠፋ ለት ፥ የጉንዳን ወረራ ፥ ትዳርን ያፈርሳል ። ---------//---------- ( በርናባስ ከበደ ) @quotes_entertain @quotes_entertain Join & share 5.5K views19:37