2022-07-08 11:58:06
በአንድ ወቅት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ከሰሃቦቻቸው ጋር በጉዞ ላይ ሳሉ ፍየል እንዲታረድ አዘዙ፤ ከእነሱም አንዱ ሶሃባ ማረዱ የኔ ፋንታ ነው አለ፤ ሁለተኛው ቆዳውን መግፈፍ የኔ ፋንታ ነው አለ፤ ሶስተኛው ደግሞ መቀቀሉ (ስጋ ማብሰሉ) የኔ ፋንታ ነው አለ።
ረሱሊ በበኩላቸው "ለማገዶ የሚሆን እንጨት መልቀሙ የኔ ፋንታ ነው" ሲሉ ሶሃባዎቹ ያ ሃቢበላህ! እኛ እንበቃለን በሚሏቸው ወቅት እንዲህ አሉ:
"እንደምትበቁ አውቃለሁ ነገር ግን ከእናንተ የተለየ ክብር እንዲኖረኝ እጠላለሁ" ብለው እንጨት መልቀም ጀመሩ የኔ ነቢይ
መሪነት ከመተናነስ ጋር ካልተጣመረ፤ ስራችንን ወረድ ብለን መስራት ካልቻልን፤ ስምና ዝና አስሮ ከያዘን መለስ ብለን እራሳችንን ልንፈትሽ እንደሚገባ የሚያስታውሰን ታሪክ ይመስለኛል።
ዙልሂጃ ዘጠኝ ላይ እንገኛለን፤ በአሁኑ ሀጁን ባንወፈቅም የሚባሉትን ዚክሮች ግን ከማለት አንዘናጋ!
ሱበሃነላህ...አልሃምዱሊላህ...ላ ኢላሃ ሃ ኢለላህ...አላሁ አክበር
اللهم صلى وسلم وبارك على نبينا محمد
#መልካም_ጁመዐ
@el_captaino18
@osmanEthiopia
የ ዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/channel/UCGRP4oXIVqSYkhg76cZbAdw
5.6K views£ℓ➶çãptâɨñø , edited 08:58