Get Mystery Box with random crypto!

የጥሪ ማስታወቂያ #OdabultumUniversity በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በኦዳ ቡልቱ | Oda Bultum University

የጥሪ ማስታወቂያ
#OdabultumUniversity

በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 8 እና 9 ሲሆን ምዝገባ የሚካሄደው ግንቦት 10 እና 11 ይሆናል፡፡

ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡-

የ8ኛ ክፍል ሰርትፊኬት ኦርጅናልና ኮፒ
የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ኦርጅናልና ኮፒ

ከ9-12ኛ ክፍል የተማራችሁበት ትራንስክሪብት ኦርጅናልና ኮፒ

አራት ፓስፖርት ሳይዝ ጉርድ ፎቶ ግራፍ እንዲሁም

አንሶላ፣ የስፖርት ትጥቅ፣ የትራስ ጨርቅ እና ብርድ ልብስ በመያዝ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ በሚገኘዉ ዋናዉ ካምፓስ በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ለበለጠ መረጃ www.obu.edu.et ወይም https://t.me/OBURegistrar ይጎብኙ

የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት

        ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን