Get Mystery Box with random crypto!

ሰበር ዜና ከወደ ግንባር የጁንታው ሃይል በሰው ማእበል ተጠቅሞ ውጊያ በማካሄድ የወረራ ህልሙን ለ | Natinael Mekonnen

ሰበር ዜና ከወደ ግንባር

የጁንታው ሃይል በሰው ማእበል ተጠቅሞ ውጊያ በማካሄድ የወረራ ህልሙን ለማሳካት ጦርነት መክፈቱን ተከትሎ የወገን ሃይል በተከታታይ እየተወሰደ በሚገኘው የጸረ ማጥቃት እርምጃ ትላልቅ ድሎች እየተመዘገቡ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን በትላንትናው ምሽት ደግሞ ከሁሉም በላይ የጦርነቱን ሂደት የሚቀይር እርምጃ መወሰዱን ከታማኝ ምንጮች የተገኘ መረጃ ይጠቁማል።

የወገን ሃይል የጠላት አመራሮች የሚያድርጉትን እንቅስቃሴ 24 ሰዓት እየተከታተለ በተመረጡት ላይ ኢላማ ተኮር እርምጃ በመውሰድ ላይ የሚገኝ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም ትላንት በተወሰደው የአየር ጥቃት ኮረም ከተማ ውስጥ በስብሰባ ላይ የነበሩ ከአምስት በላይ የጁንታው ቁልፍ አመራሮች መደምሰሳቸውን የሚገልጽ የብስራት ዜናዎች ተሰምተዋል።

ከነዚህ አመራሮች መካከል
ጀ/ል ጻድቃን ገ/ትንሳይ፣
ጀ/ል ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ)፣
ጀ/ል ዩሃንስ (መዲድ)፣
ጀ/ል ከበደ ሸሪፎ፣
ጀ/ል አብረሃ ድንኩል እና ወዲ አባተ በወቅቱ ስብሰባ ላይ ከነበሩት አመራሮች መካከል ይገኙበታል። አመራሮቹ ለጥንቃቄ ሲሉ በአንድ ብዙም የማያስጠረጥር ግቢ ውስጥ በአንድ ጠረቤዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ስብሰባ እያደረጉ ባሉበት ሁኔታ እርምጃው የተወሰደ በመሆኑ ከወዲ አባተ በሰተቀር ሌሎቹ የተደመሰሱ መሆናቸውን የሚገልጽ መረጃ ተገኝቷል።

በዚህም የተደናገጡ የጁንታው አመራሮች ጉዳዩ በህወሃት ደጋፊዎች እና ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ የስነልቦና ጫና እንደሚፈጥር በመገንዘብ ጉዳዩን ለጊዜው በጥብቅ ሚስጢር በድብቅ ለመያዝ መወሰናቸውን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።