የፈጅር (የሱብሒ) ሶላት የደረሰ ጊዜ «ተነስ! ሂድና መስጅድ ስገድ!» አለችው። «እዚሁ ነው የምሰግደው!» አላት። «ሸሪዓውኮ ወንዶች መስጅድ ሂዳችሁ በጀማዓህ እንድትሰግዱ አዟል!» አለችው። «ሸሪዓውማ ከ1 በላይ እስከ አራት ማግባትንም ፈቅዷል!» አላት። እርሷም ፈጠን አለችና «መስገጃውን እዚህ ላንጥፍልህ ወይንስ ሳሎን?» አለችው። ከዚያ በኋላ ምን እንደተከሰተ አልሰማሁም¡ (የሰሙ ሰዎች ከሱ-ንናው ይልቅ ፈርዱን ላስቀድም ብሎ መስጂድ ሂዶ ሰግዷል ብለውኛል። ከፈርዱ ባሻገር ሱ-ንናውን ስለመተግበሩ ግን እነርሱም የሰሙ አይመስለኝም¡) 9.3K viewsedited 15:15