ኢንተር ሚላን የሴሪኣው ሻምፒዮን ለመሆን ተቃርቧል !
ትላንት ምሽት በ 31ኛ ሳምንት የጣሊያን ሴሪኣ መርሀ ግብር ከሜዳው ውጪ ዩዲኒዜን የገጠመው ኢንተር ሚላን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
በዚህም ምክንያት ኢንተር ሚላን ሊጉን ከተከታያቸው ኤሲ ሚላን በ 14 ነጥብ በመብለጥ እየመሩ ይገኛሉ።
የጣሊያን ሴሪኣ ሊጠናቀቅ 7 ጨዋታዎች ብቻ የሚቀሩ ሲሆን ኢንተር ሚላን በቀጣይ ሁለት ጨዋታዎችን የሚያሸንፋ ከሆነ የሴሪኣው ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል።
አስደናቂ ብቃት ላይ የሚገኘው ኢንተር ሚላን በ 2024 በሴሪያ ካደረጋቸው 13 ጨዋታዎች 12 አሸንፎ 1 አቻ ወጥቷል።
SHARE @MULESPORT