Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያን ነገር….. አባ አባ ብዬ - በለመንኩህ ለቅሶ - ተሰምቷል ጩሀቴ በውን ያ | መንፈሳዊ ግጥም ብቻ

የኢትዮጵያን ነገር…..

አባ አባ ብዬ - በለመንኩህ ለቅሶ - ተሰምቷል ጩሀቴ
በውን ያስጨነቀኝ - ተራራው ፈተና - ተነስቷል ከፊቴ
የተማመንኩበት - የሥምህ ስንቅነት - አንዳች አልጎደለ
ተስፋ ያደረግሁት - የጸሎትህ ሥምረት - በሕይወቴ አለ
የተደገፍኩበት - የደጅህ ዋስ’ነት - ሜዳ አልጣለኝም
እንባ የረጨሁበት - የ’ስማኝ!’ ዋይታዬ - አልወደቀብኝም
ከህጻንነቴ - አንተን ተማምኜ - የሄድኩበት መንገድ
በጥቅጥቁ ጫካ - አንበሳው አልነካኝ - አልሆንኩ አልቦ ዘመድ
ልጅነቴ ሁሌ - ገብረ ሕይወት እያለች -በምልጃህ ተማምና
ትናንት እንዳልተውካት - ዛሬም ስትጣራህ -ለነፍሴ ጭንቅ ና፡፡

Abboo! - Aabboo! ብዬ - ሀገር አሻግሬ - ስምህን እጠራለሁ
ከግብጽ በረሃ - ለምትሻህ ኢትዮጵያ - ቶሎ ና እላለሁ
ታስፈልጋታለህ - እንኳንና ለሰው - ለአናብስት ሁሉ
የጽድቅህን ፍሬ - የቀመሱ ነፍሳት - አባ አባ ይላሉ
የንጽኅናህ ግርማ - ከግብጽ እስከ ኢትዮጵያ - ሀገር እያወደ
አንበሳውም ነብሩም - እያገለገለህ፣- አንተን እያጀበ- ካንተ ጋራ ሄደ፡፡
አቡዬ ና ድረስ- ና ገስግስ ዘንድሮም - ቶሎ ና ለሀገሬ
እረፉ በላቸው - እንዳይናከሱ - ሰውንና ሰውን - ሰውንና አውሬ፡፡

ዛሬም ቁም ዝቋላ - ግባ ከባህሩ - እጆችህን ዘርጋ
ፈልግ ልጆችህን - የጸሎት ፍሬህን - የጠበቅኸውን መንጋ
ከሰሜን ከደቡብ - ከምስራቅ ከምዕራብ - የተጋደልህለት
“ኢትዮጵያን ማርልኝ !” - ብለህ ከአምላክህ ፊት - ብዙ የጸለይክለት
የረገጥከው መሬት - ያረፍክበት ደብር - የነካህ አፈሩ
ዳግም በዛሬው ቀን - ጸሎትህን ይሻል - መላው ሀገሩ
ምድረ ከብድ ድረስ - ተገኝ በዝቋላ - አንሳ እጆችህን
እስከምንጠገን - ተሰብረናልና - እየን ልጆችህን
አታሳፍረንም - ገብረ መንፈስ ቅዱስ - ብለን ስንጠራህ
እንግዲህ አቡዬ - የኢትዮጵያን ነገር - አሁንም አደራህ!!