ግሸን ማርያም ! ።።። ኤልያስና ኤልሳ በእድሜ ገርጅፈው ልጄ ማይሉትን... ደፍረው ማይቀርቡትን... አቅፋ ስማዋለች በ አስራምስት ዓመቷ ድንግል ወላዲቷ . ሰዎች ውሸት አሉ ማረጓ ተናቀ ግና... አዲስ ሰማይ አይቶ ሰማይ ተደነቀ . በማህፀን እሳት ... መለኮትን ማጀብ አጀብ! . የዓለም ትልቁን በማህፀን ይዛ ማማለድ አትችልም አለኝ ያ ፈዛዛ አሁን ምን ይሉታል ለትልቁ ታጭቶ ትንሹን መከልከል እንደዚህም አይደል ! . አለቀብን ወይን ሳሳብን ማጀቱ እሱ ግን ባረከው ስትነግረው እናቱ ቅጠል ለቅሞላታል ያኔ ህፃን ሳለ ወላጅህን አክብር ይሉት የኦሪት ህግ እንዲሁ ቀጠለ... . ተከትዬህ ከጫፍ መስቀልህ ስር ቆሜ በመለየት ፍርሀት በፅኑ ታምሜ ሳለቅስ ሲከፋኝ ስደበት ሳነባ ድንግልን ሰጠኸኝ የሞገሴን ካባ ! Michael Aschenaki @Mgetem @Mgetem 1.7K viewsSol, 07:29