Get Mystery Box with random crypto!

ስፖርት ዞን sport zone

የቴሌግራም ቻናል አርማ mekusaied123 — ስፖርት ዞን sport zone
የቴሌግራም ቻናል አርማ mekusaied123 — ስፖርት ዞን sport zone
የሰርጥ አድራሻ: @mekusaied123
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.51K
የሰርጥ መግለጫ

sport zone

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 74

2022-09-18 21:03:38
#ፎቶ

√ የስፖርት ዞን የአትሌቲክስ ዘርፍ አሸናፊዎች ሲገለፅ በወንዶች ዘርፍ በኦሪጎን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በማራቶን ወርቅ ለሀገሩ ያስገኘው ታምራት ቶላ ልዩ የአትሌቲክስ ዘርፍ አሸናፊ ሆኖ ተመርጧል።

√ በህክምና ዘርፍ በአሁን ሰዓት በርካታ ስፖርተኞች ከሀገር ውጪ ሳይወጡ በሀገራቸው ህክምና እንዲያደርጉ የበኩላቸውን እየተወጡ የሚገኙት ዶ/ር ማሞ ደቅሲሳ በአሸናፊነት ተመርጠዋል።

√ በ 2014ዓ.ም የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ካስተናገዱ ከተሞች መካከል ባህርዳር ከተማ ደማቅ ዝግጅት በማስተናገድ በስፖርት ዞን ሽልማት ሰባተኛው ዘርፍ አሸናፊ ሆነዋል።
4.1K viewsKidus, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:43:50
#ፎቶ

√ የስፖርት ዞን የ 2014ዓ.ም የአመቱ ምርጥ ጎል አሸናፊ ሲገለፅ ኤርትራዊ የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ሮቤል ተክለ ሚካኤል በሰበታ ከተማ ላይ ከርቀት ያስቆጠራት ግብ በአሸናፊነት ተመርጣለች።

√ የሉሲዎቹ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፊት መስመር ተጫዋች ሎዛ አበራ እውቅና ሲበረከትላት የምስጋና ተሸላሚ ሆና ተመርጣለች።
2.9K viewsKidus, 17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:31:46
የ 2014 የስፖርት ዞን የአመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግን ያሸነፈው ጋቶች ፓኖም በአመቱ ምርጥ ተጫዋች ዘርፍ አሸናፊ ሆኗል።
2.3K viewsKidus, 17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:28:09
የ 2014 የአመቱ ምርጥ ደጋፊ ዘርፍ የባህር ዳር ከነማ ደጋፊዎች አሸናፊ ሆነዋል።
2.3K viewsKidus, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:27:17
የ 2014 የስፖርት ዞን የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ በመባል ቅዱስ ጊዮርጊስ የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሻምፒዮን ያደረገው አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ በአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ዘርፍ አሸናፊ ሆኗል።
2.1K viewsKidus, 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:21:07
የ 2014 የስፖርት ዞን የአመቱ ግብ ጠባቂ በመባል ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግን ያሸነፈው ቻርለስ ሉክዋጊ በአመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂ ዘርፍ አሸናፊ ሆኗል።
2.0K viewsKidus, 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:20:06
የ 2014ዓ.ም የስፖርት ዞን የአመቱ ምርጥ ምስጉን ዳኛ ዘርፍ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ዶ/ር ሀይለየሱስ ባዘዘው በኮከብ ዳኝነት አሸናፊ ሆኗል።
2.0K viewsKidus, 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:15:07
የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ይፋ ሆኗል !

የ 2014ዓ.ም የስፖርት ዞን የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች በአሁን ሰዓት ይፋ ሲደረግ በሐዋሳ ከተማ የውድድር ዘመኑን ያሳለፈው ብሩክ በየነ አሸናፊ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ከ 23ዓመት በታች ዋና አሰልጣኝ አጥናፉ አለሙ ለአሸናፊው ብሩክ በየነ ሽልማቱን አበርክተዋል።
2.0K viewsKidus, 17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:15:07
የ 2014 የስፖርት ዞን ሽልማት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የስፖርት ዞን የታሪክ አሻጋሪ የሆኑ ግለሰቦችን እውቅና ሲሰጥ ስድስት ግለሰቦችን ተሸላሚዎች አድርጓል።

በዚህም መሰረት :-

በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚንስተር አቶ መስፍን ቸርነት ፣ የፌዴሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ጨምሮ የስፖርቱ ቤተሰቦች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

በመጀመሪያው የሽልማት ስነ-ስርዓት የአፍሪካን የነፃነት እግር ኳስ ያጀቡ አፓርታይድን በስፖርቱ የተዋጉት ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የታሪክ አሻጋሪ ሽልማት ሲያሸንፉ ልጃቸው አማካኝነት በስፍራው ተረክቧል።

ከዚህ ባለፈም ከሐዋሳ ከተማ ጋር የመጀመሪያውን የሊግ ዋንጫ ያሳኩት እና በብሔራዊ ቡድን በረዳት አሰልጣኝነት የሰሩት አሰልጣኝ ከማል አህመድ ሌላኛው የታሪክ አሻጋሪ ተሸላሚ ሆነዋል።

ሶስተኛው የታሪክ አሻጋሪ ተሸላሚ የሆኑት በአትሌቲክሱ ዘርፍ እንደ ሀይለ ገ/ስላሴ ፣ ደራርቱ ቱሉ እና ብርሀኔ ሀደሬ የመሳሰሉ ሯጮችን ለሀገሪቱ ያበረከቱት ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ተሸልመዋል።

ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ሀገራቸውን በአምስት ኦሎምፒክ ሲመሩ ሀያ ስምንት ሜዳሊያዎችን ሲያስገኙ የስፖርት ዞን የታሪክ አሻጋሪ ተሸላሚ ሲሆኑ በህይወት ባይኖሩም ልጃቸው ያቆብ ኮስትሬ በስፍራው የአባቱን ሽልማት ተረክቧል።

በአራተኛ የታሪክ አሻጋሪ ሽልማት አሸናፊ ዘርፍ ጋዜጠኛ እና የእግር ኳስ ታሪኮችን ሰንዶ ያዘጋጀው ገነነ መኩሪያ ተሸላሚ ሆኗል።

በአምስተኛው የታሪክ አሻጋሪ የህይወት ዘመን ሽልማት በአትኬቲክሱ ዘርፍ በኦሎምፒኩ የሀገሩን ባንዲራ ያውለበለበው ምርፅ ይፍጠር ሲሸለም ልጁ ቢንያም ምርፅ በስፍራው በመገኘት ሽልማቱን ወስዷል።
2.4K viewsKidus, 17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 18:11:27
ፋሲል ከነማ ድል ቀንቶታል።

በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ ቡማሙሩን የገጠሙት አፄዎቹ 3ለ0 አሸንፈዋል።
አለምብርሀን ይግዛው
ፍቃዱ አለሙ
ታፈሰ ሰለሞን ግቦቹን አስቆጥረዋል።
2.3K viewsSolbek, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ