መቻል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝተዋል !
በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመሩት መቻል ከመመራት ተነስተው 3ለ2 በሆነ ውጤት ባህር ዳር ከተማን በመርታት ደረጃቸውን አሻሽለዋል።
√ በረከት ደስታ ፣ ከንዓን ማርክነህ እና በሀይሉ ግርማ የመቻልን የማሸነፊያ ጎሎች ከመረብ አሳርፈዋል።
√ ዱሬሳ ሹቢሳ እና ኦሴ ማውሊ የጣና ሞገደኞቹን ሁለት ጎሎች አስቆጥረዋል።
√ ዱሬሳ ሹቢሳ በውድድሩ ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ መጠን ወደ አምስት ከፍ አድርጓል።
√ ከንዓን ማርከነህ ለአዲሱ ክለቡ መቻል የመጀመሪያ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።
√ መቻል በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በአስራ ስድስት ነጥብ #ስምንተኛ ላይ ሲቀመጡ አንድ ቀሪ ጨዋታ የሚቀራቸው ባህር ዳር ከተማዎች በሀያ ሁለት ነጥብ #ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።