ኦሊቨር ጂሩድ ትላንት በልምምድ ላይ ባጋጠመው መጠነኝ የጉልበት ህመም ምክንያት በዛሬው ጨዋታ ላይ በቋሚነት የመሰለፉ ነገር አጠራጣሪ እንደሆነ የፈረንሳዩ ጋዜጣ ሌኪፕ ዘግቧል ።
ከኦሊቨር ጂሩድ በተጨማሪም ራፋኤል ቫራንም በዛሬው ጨዋታ በቋሚነት ላይጀምር እንደሚችል በስፋት እየተዘገበ ይገኛል ።
Rmc Sport በበኩሉ የፈረንሳዩ አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾ ኦሊቨር ጂሩድን በተቀያሪ ወንበር ላይ በማስቀመጥ ኪሊያን ምባፔን በዘጠኝ ቁጥር ቦታ ለማሰለፍ እና ማርከስ ቱህራምን በግራ ክንፍ በኩል ለማጫወት እያሰቡ እንደሆነ በዘገባው ላይ ገልጿል ።