Get Mystery Box with random crypto!

...

የቴሌግራም ቻናል አርማ maryamawithenok — ... M
የቴሌግራም ቻናል አርማ maryamawithenok — ...
የሰርጥ አድራሻ: @maryamawithenok
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 748

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-27 09:47:44 Channel name was changed to «...»
06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 17:20:52 The Man who Said No, Finally Wins.

ከወር በፊት ፥ ኢትዮጵያ በጦር ሜዳም በዲፕሎማሲውም ሜዳ የተሸነፈችና መጨረሻዋ የደረሰ ይመስል የምዕራባዊያን ሚዲያዎች ሙሾ ያወርዱ ነበር። ሀገሪቷም ቀጣዯ ሶሪያ አልያም ሊቢያ ፥ መሪዋም የሞኣመድ ጋዳፊና የሳዳም ሁሴን እጣ ይደርሰዋል ትንታኔ አየሩን ተቆጣጥሮት ነበር።

''ከእንግዲህ እኔ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ከነገ ጅምሮ ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ። ታሪክ ከሚያደንቃቸው የኢትዮጵያ ልጆች አንዱ ለመሆን የምታስቡ ሁሉ ለሀገራችሁ ስትሉ ዛሬውኑ ተነሡና፤ ግንባር ላይ እንገናኝ፡፡ "

ይህ ጠ/ሚ አብይ ከሰጠው መግለጫ መደምደሚያው ነው። ጠቅላዩ የመጨራሻ የሚመስል ቃሉን ሰጥቶ ብቻውን አይደለም ሚሊየኖቹን አስከትሎ ወደ ግንባር ተመመ። ሲያክልም፦ ''ግንባር ላይ እያዋጋ የምንፈልገው ኢትዮጵያዊ ወይም ኢትዮጵያን መሆን ነው አለን። ኢትዮጵያዊ ሆኖ መኖር፣ ኢትዮጵያን ሆና መቀጠል፣ ወይም ደሞ ኢትዮጵያ መሬት ላይ ኢትዮጵያዊ ሆነን መሞትን።'' ይህ ብቻዉን ለጠላት የባላስቲክ ሚሳኤል ያክል ነበር።
...
በሳምንት ውስጥ ጠላት አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ አብዝሀኛው እንዳይመለስ ተደርጎ ሲሸኝ ፥ ቀሪው ወደ መጣበት የዃላ ማርሽ አስገብቶ እንዲፈረጥጥ ሲደረግ። የጦርሜዳው ድል በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊያን ብሎም በመሪዋ እጅ መግባቱ የታመነ ነበር። ቀጣዩ ፍልሚያ የዲፕሎማሲው ነበር። ያለማቋረጥ በአራቱም ማዕዘን ያሉ ኢትዮጵያዊያን በተሳተፉበት ሰፋፊ ንቅናቄ አንድም የኢትዮጵያ እውነት ለዓለም ሁሉ እንዲገለጽ ፣ አንድም በዲፕሎማሲው መስክና በመንግስት ህዝባዊ ቅቡለት ያለማጠራጠር መንግስት ዳግም በትሩን እንዲቆጣጠር አስችሎታል። በተጨማሪም በተከታታይ መንግስት በወሰዳቸው ርምጃዎች ምንም እንኳ ቅር የተሰኘ ብዙ ቢኖርም በመጨረሻ ግን ኢትዮጵያ የጠቆረ ምስሏን እንድትጠርግበት አስችሏታል።
...

ዛሬ፥ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ተከባለች አበቃላት ስትባል በነበረች አዲስ አበባ ሲጀመር ፥ ሀገሪቷም በሁሉም መስክ አሸንፋና የተነዛባትን ፕሮፖጋንዳ ቀልብሳ ሰላማዊት መሆኗን ስታስመሰክር ፣ መሪዋም እንደተቀሩት Puppet leaders አንድም ክፉ እጣ ደርሶት እንደከዚ ቀደሞች ጥቁር መሪዎች ወደ ጎረቤት ሀገር ሸሽቶ አልያም ለምዕራባዊያን ተገዝቶና ተሰብሮ ሳይሆን ለሀገሩና ለህዝቡ የታመነ ጥቁር መሪ ሆኖ በኩራት በተቀሩት ሁሉ ፊት ቆሞ ፥ ከኢትዮጵያ ከፍ ብሎ ስለ አፍሪካና አፍሪካዊያን ድምጹን አሰምቷል። The Man who Said No, Finally Wins.
....
Maryamawit Henok
909 views14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 17:20:49
636 views14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 08:10:06 ይህን መጽሐፍ አንድ ወዳጅ ጠቁሞኝ ማንበብ ጀመርኩ... ግሩም ነው፤ አላገባደድኩትም ነገር ግን አጋምሼዋለሁ። እምብዛም ያልተለመደ አየነት የምንለው ነው። በተገኘበት ይነበበ! -) አይነት ፍርድ የሚገባው ክታብ ።
መጽሐፉን ፥ ሁሉ እንዲያነበው ብመክርም (ያለ ሀይማኖት ልዩነት)፤ ከፍ ብዬ ግን ፥ የታሪክ፣ የፍልስፍና፣ እና የቴዎሎጂ እንዲሁም የንጽጽር ሐይማኖት ፍላጎት ላላችሁ ደግሞ ከቤታችሁ ሊታጣ የማይገባ መጽሐፍ ነው እላለሁ።
...
አንድ ወዳጃችን እንዳለው ''ሥርዓት ባለው መልኩ ተዋሥኦ ማድረግ የጤና ነው''። “በአቸንፋለው፤ እናቸንፋለን” ግትር አቋም ብቻ የሚደረግ ክርክር ፍጻሜው ሻሞላ ያማዝዛል፥ ሕዝብ ለእልቂት፤ አገር ለውድመት ይዳርጋል። በክርስትና-እስልምና ቀደምት ተዋሥኦ ውስጥ እጅግ ድንቅ የሆኑ የነገረ መለኮት ትምህርቶች ነበሩ፤ ለዘመናት ግን ተመልከች አጥተው፥ ተገፍተው ነበር። አብርሃማዊ በሚባሉት፥ ይሁዲ፣ ክርስትና፣ እስልምና መካከል ይደረጉ የነበሩ ተዋሥኦች ጥናት ሊደረግባቸው ይገባል። ዲ/ን በረከት አዝመራው በዚህ በኩል አንድ ሸጋ መጽሐፍ ሸልሞናል። በክርስትና-እስልምና መካከል ይደረጉ የነበሩትን፥ ከ7ኛ መቶ ክፍለ ዘመን ወዲህ ያሉትን ተዋሥኦ በጥሩ ዝግጅት አቅርቦልናል።

ዕቅበተ እምነትን/Apology/ ከርዕዮተ ዓለማዊ የሥነ ሕዝብ ፍልስፍና/Political Ideology/ በጠራ መልኩ መረዳት የዘመናችን ችግር ነው። ዘርን፤ ቋንቋን መሠረት እያደረጉ ዕቅበተ እምነት በሚመስል መልኩ፥ ፖለቲካ የተንተራሰ ትንኮሣ በክርስቲያኖች ላይ የሚያደርጉ የእስልምና እምነት ተከታይ ወንድሞቻችንን መታዘብ ችለናል። ከዚህ “የእኛ ብቻ ትክክል” ከሚል ደርዝ ከሌላው አካሄድ በመላቀቅ÷ ቀደምት ሥራዎችን መመርመር ያስፈልጋል። በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “መጽሐፍ ቅዱስን ተርጉመን እናስጠናችሁ፥ የአምላካችሁን ማንነት እንግለጥላችሁ” የሚሉ ደፋር የእስልምና እምነት መምህራን በተደጋጋሚ ይደመጣሉ። ለእነርሱ የስሕተት ሐቲት፥ ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ ለመሥጠት የሞከሩ አበው ደግሞ ተንኳሽ ተብለው ተወግዘዋል፤ ተሰድበዋል። እኛ አፍ፥ እናንተ ጆሮ ብቻ ሁኑ ከተባልን ሰንብተናል!!
625 views05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 08:09:55
448 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 08:09:19 የብሄር ወንድሞቻቸውን የተለያየ ስም እየሰጡ ከቀድሞው ስርአት ጋር አብረው የሚወጉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ስልጣን የያዘውን ወንድማቸውንና አንድ ሰሞን ሰማየ ሰማያት አድርሰውት የነበረውን ሰው በተራ የሶሻል ሚዲያ ነፍጠኛናው ኤርትራዊ ነው ዘለፋ እና ማንነት ቀመታ እስከ ጫካ የገባና የታጠቀ አማጺ ቡድን ተሰልፋል።

ከኦሮሞ ብሄር የወጡ ልጆች ስልጣኑን የተቆጣጠሩ ሰሞን የሁሉም ህዝቦች ተስፋ የለመለመበት ሙሉ ድጋፉንም የሰጠበት ነበር። አሁን ግን በእርስ በርሳቸው ሽኩቻና አለመስማማት በአንድ ቀን በመቶዎች የሚቆጠሩ የሌላ ብሄርና የክርስቲያኖች ህይወት የሚቀጠፍበት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ መኖሪያና የንግድ ተቋማት የሚቃጠሉና ህዝቦች የሚሰደዱበት አስፈሪ ጊዜ ተፈጥሯል። የዚህ ዋነኛ ተጎጂና ገፈት ቀማሽ ደግም ንጹሃኑ የኦሮሞ ህዝብ ሆኖ ሲታይ ምን አይነት እድለቢስነት ነው ያስብላል።

የኦሮሞ ፖለቲካ Golden የተባለ ጊዜውን አስበልቶ ሲያበቃ አንዴ በነፍጠኛ ሌላ ጊዜ በወያኔ እያሳበበና እያለቀሰ ቁጭ ብሏል። ታሪክ ግን ሲያስታውስ የሚያስታውሰው የአንድ ብሄር ተወላጆች ለስልጣን በሚያደርጉት ሽኩቻና መከዳዳት ይሄ ወርቃም የልሂቃን ዘመን እንደከሸፈ ነው። ያለውን ልዩነት አቀራርቦና አስማምቶ መሄድ ካልተቻለ፤ የወጡበት ህዝብንና አፉን በእጁ ጭኖ እየተመለከታቸው ያለውን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ እየመለሱና ከዚህ እእከፊ የድህነት ህይወት መውጣት ካልቻሉና አሁን ባላቸው የእርስ በርስ መራኮት ከቀጠሉ ታሪክ ሲያስታውሳቸው The failed Oromo golden political generation እያለ ይሆናል።
...
Maryamawit Henok Tipi
420 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 08:09:19 The Golden political generation, Failed ?

በኦሮሞ ልሂቃን መካከል ንግግር ለማድረግ ሽርጉዱ ተጀምሯል።አንድ ሁለት ሶስቴ ውስጥ ለውስጥ ሙከራዎች መካሄዳቸውንና ይሄ ነው የሚባል የጎላ ነገር እንዳልተገኘ ቢታወቅም፤ ለቀጣዩ ግኔ እንደሚሳካ ተስፋ በማድረግ ከሁለት ዓመት በፊት በወቅቱ የነበረውን የኦሮሞ ልሂቃን ፍትጊያ ለማሳየት ሞክሬ ነበር፤ አሁን ሙሉ ለሙሉ የሀይል ሚዛኑ ተጠቃሎ የዶ/ር አብይ እጅ ላይ የገባ ቢሆንም ወደ ዃላ መለስ ብለን ስናስተውለው ግን አሁን የሆነው ሁሉ የሚሆን አይመስልም ነበር። ጊዜውን ማስታወስ ለሚሻ ቀጣዩን ጽሁፌን ያንብብ -)
...
የኦሮሞ ፖለቲካ በዚህ ዘመን የገጠመው አይነት የልሂቃን ስብስብ ገጥመውት የሚያውቅ አይመስለኝም ፈጽሞም። ይሄ 𝐎𝐫𝐨𝐦𝐨 𝐆𝐨𝐥𝐝𝐞𝐧 𝐏𝐨𝐥𝐢𝐭𝐢𝐜𝐚𝐥 𝐀𝐠𝐞 የሚባለው አይነት ነበር። ነገር ግን እርስ በርስ መስማማት አቅቷቸው በኢትዮጵያዊያን ሁሉ ድጋፍ ይዘው፤ ከስልሳዎቹ ትውልድ እስከ ቁቤ ጀነሬሽን የደረሰ፣ ከኦነግ መስራቾቹ ሌንጮ ለታ፣ ዶ/ር ሌንጮ ባቲ፣ ዳውድ ኢብሳ.... እስከ ጀነራል ከማል ገልቹ፤ ከዶ/ር መራራ ጉዲና እስከ ዶ/ር አብይ፣ ለማ መገርሳ፣ ጃዋር፣ ታከለ ኡማ የደረሰ የተለያየ የእድሜ የብቃት፣ የአተያይ፣ የተቀባይነት ደረጃ ያላቸው ልሂቃንን የያዘ ትውልድ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የብሄሩን ፖለቲከኞች ይዞ ስልጣን ቢይዝም ቅሉ አብሮ በመስራት በመስማማተሰ ሊዘልቅ የቻለው ወራትን ብቻ ነው። ይሄ ስብስብ ቢጠቀምበት ከሀገር ውስጥ ድጋፍ አስከ ዓለም አቀፍ የኖቤል ሽልማት የያዘና በምዕራባዊያኑም መልካም ስምና ሙሉ ድጋፍ የያዘ ነበር።

እነዚህ የብሄሩ ልሂቃን የመጡበትን ብሄር ብሎም መላን የኢትዮጵያ ህዝቦችን በሙሉ እምነትና ድጋፍ ይዘው ሳሉ፤ በቅናት፣ በስልጣን ጥማት፣ በአካባቢያዊነት (ጎጥ) ፣ በመሳሰሉ ርካሽ አስተሳሰቦች ተራኩተው ለመጡበት ብሄር ለመላው ኢትዮጵያዊ የጸጥታና የሰላም ስጋት የሆኑበት ደረጃ ላይ ተደርሷል።
...
በዶ/ር አብይ እና በአቶ ለማ የሚመራው መንግስት ስልጣኑን እንደያዘ ሰሞን ያደረገው ነገር የኦሮሞም ይሁን የሌላ ብሄር ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ወደ ሀገር ቤት ማስገባትና ለተወሰኑት ስልጣን ማጋራትን ነበር የመጀመሪያው እርምጃው ያደረገው። የኦነጉን ጀነራል ከማል ገልቹን የኦሮሚያ ጸጥታና ደህንነት ሃላፊ፣ የኦነግ መስራቾቹን ዶ/ር ሌንጮ ባቲ እና አቶ ሌንጮ ለታ የጠ/ሚ አማካሪ፣ጃዋር ምሃመድንም ቢሆን ይሄ ነው ተብሎ በይፋ ያልተገለጸ ነገር ግን ሶስቱ በጋራ እየተመካከሩ እየሰሩ እንዳሉ የሰላሙ ሰሞን እራሱ ጃዋር እንደተናገረ ይታወስ፣ ሌሎች ብዙ የኦሮሞ ተቃዋሚ የነበሩ በክልሉም በፌደራልም ስልጣን ይዘው እንዲመሩ ተደረገ።
...
የመጀመሪያው ፍትጊያ በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራ ኦነግ እና በአቶ ለማ መገርሳ ከሚመራው የኦሮሚያ ክልል በዃላም ከፌደራል መንግስቱ ጋር ገጠመ። አቶ ዳውድ ታጣቂዎቻቸውን ማን ፈቺ ማን አስፈቺ ስሉ በአንድ ሀገር ሁለት የታጠቀ ሀይል እንደሚኖር በድፍረት ተናገሩ። እነሆ ወለጋ ላይ የመጀመሪያው መሳሪያ መማዘዝ በኦሮሞ መሪዎችና በኦሮሞ ተቃዋሚዎች ተጀመረ። በጊዜው ጃዋር አሰላለፉን ከነ ዶ/ር አብይ ጋር በማድረግ የአቶ ዳውድ ኢብሳን ዘገን ትጥቅ እንዲፈታ በህዝብ ፊት ያሳጣ በቃላትም ይጠዘጥዝ ነበር።
...
ሁለተኛው ልዩነት በዶ/ር አብይ እንዲሁም በለማ መገርሳ የሚመራ መንግስትና ስልጣን ሊያጋራ ከውጭ አስገብቶ የኦሮሚያ ክልል የጸጥታና ደህንነት ዘርፍ አላፊ ባደረጉት ጀነራል ከማል ገልቹ መካከል ሆነ። ጀነራል ከማል ገልቹ በተመሳሳይ ጊዜ በአቶ ዳውድ ኢብሳ ከሚመራው ኦነግ ጋር ሌላ ከባድ ጸብ ነበርው። እንደውም የአቶ ዳውድ ኦነግ በመንግስት ላይ ማቄም የጀመረው እንዴት እኛን ጥሎ የጀነራል ከማል ገልቹን እነግ አስጠጋ ከሚል ነው። ወደ ቀደመነገራችን ስንመለስ ጀነራል ከማል ገልቹ ለክልሉ ፕሬዘዳንት ለማ መገርሳ አልታዘዝ በማለት የራሱን መዋቅር በክልሉ ደህንነትና ፖሊስ ላይ መገንባት ጀመረ። አያያዙ አላምር ያለው የክልሉ ፕሬዘዳንት ለማ መገርሳ የኦዴፓ ስራ አስፈጻሚም ሆነ ማዕከላዊ ኮሚቴ ሳያውቅ በሁለት መስመር ደብዳቤና በራሱ ቲተርና ፊርማ ከስልጣኑ አባረረው። ጀነራል ከማል ገልቹ የወራት ያህል ቆይቶ በዃላም ተጣልቶ የወጣበትን የመንግስት ሚስጥር በየሚዲያ ይነዛው ጀመር።
..
ሶስተኛው በጃዋር ሞሃመድና በኦዴፓ ባለስልጣናት የጀመረ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ጋር የደረሰ ነበር። ጃዋር እነ ዶ/ር አለሙ ስሜን፣ እነ ታዬ ደንደአን... ወዘተ በአደባባይ ስም ሲያጠፋና ሲዘረጥጥ የተመለከቱ አስከትሎም ከዃላ በነ ጠቢባ ሀሰን በኩል ሊዘውራቸው እንደፈለገ የገባቸው ዋናዎቹ ዶ/ር አብይ እና ለማ መገርሳ የፊት ለፊት ጸብ ከጃዋር ጋር ገጠሙ። ሰንሰለቱን ለመበጣጠስ በሚል ወ/ሮ ጠቢባ ሀሰንና የመሳሰሉ የክልሉ ክፍተኛ ባለስልጣናትንና የከተማ አስተዳደሮች ከስልጣናቸው በማንሳት አየር ላይ አንሳፈፉ። ጃዋርም በሚዲያውና በጀሌዎቹ ታግዞ የስም ማጥፋት ዘመቻውን ተያያዘው። በኦዴፓ ውስጥ ያሉትንና አመራሮች በመጠቀም ጠ/ሚ ዶ/ር አብይን ከኦዴፓ ሊቀመንበርነት ለማንሳት የውስጥ ለውስጥ ቅስቀሳና ዘመቻ ጀመረ፤ ዶ/ር አብይን ከኦዴፓ ሊቀመንበርነት ጨፌ ኦሮሚያ ካስነሳው ኢሚዲየትሊ ከጠ/ሚስትርነቱም ይነሳል። የተሰራው ፎርሙላ ይህ ነበር። ዶ/ር አብይ በበኩሉ ድምጹን አጥፍቶ ውስጥ ለውስጥ እንዴት እንደሰራው በማይታወቅ ሁኔታ 8 የክልል ፓርቲዎቹን አፍርሶና አዋህዶ ፓርቲውን መስርቶ የፓርቲው ሊቀመንበር ሆኖ ቁጭ አለ። ጨፌ ላይ የታሰበው ሴራ ላያንሰራራ ተመታ። ዶ/ር አብይ በጣም ጥቂቶች ኢትዮጵያዊም በታሪኳ አግኝታ የማታውቀውን የአለም የኔቤል ሽልማት በማድረግ በአለማ አቀፍ ደረጃ ስሙንያ ክብሩን አሳድጎ ቁጭ አለ።
...
አራተኛ ዶ/ር አብይ 8 ፓርቲዎቹን አስተባብሮ የራሱን ፓርቲ መመስረቻው ጫፍ ላይ ተሰሚነቴ ቀነሰ ሁሉም ዶ/ር አብይን ብቻ ነው የሚሰሙት... የተከዳሁ አይነት ስሜት የያዘው ለማ መገርሳ በውሰሰጡ የያዘውን ቁጣ ይዞ ወደሚዲያ ወጣ። የለማና የዶ/ር አብይ የረጅም አመት የትግል አጋርነት በወንበር ምክንያት ታላቅ ስንጥቅ ገጠመው።
....
አምስተኛ ዶ/ር አብይን ለመጣል በዘመነ ወያኔ በስደት ኤርትራ በረሃ እርስበርሳቸው መስማማት አቅቷቸው የወለጋና የአርሲ ፥ ሌላ ጊዜ የባሌ የሀርርጌ እያሉ ሲጨፋጨፉ የነበሩ ቡድኖች ተስማምተው ከአንድም ሶስት አራት ተማማሉ ተፈራረሙ። በወራት ስምምነቱ ፈርሶ እርስ በርሳቸው ወደፊት በሚኖረው የስልጣን ድልድል መጠዛጠዝ ጀመሩ።
...
አሁን ያለው ሁኔታ።
አሁን ከአንድ ማህበረሰብ ወጥተው ስልጣን ይዘው ሙሉ የህዝብ ድጋፍ ኖሯቸው በተረጋጋ ሁኔታ ሀገር መምራት ያልቻሉበት ደረጃ ደርሰዋል። ለዚህ ተጠያቂ ደግሞ እራሳቸው የኦሮሞ ተቃዋሚ ልሂቃንና ፖለቲከኞች እንጂ ሌላ ማንም አይሆንም። በቅናትና ዘለፋ የተጀመረው መነታረክ ወደ ግድያና ጦር ማማዘዝ ሄዶ የመንግስት ባለስልጣናቶች በገዳይ እስኳዶች እየታደኑ የሚገደሉበት፤ በሴራ ታዋቂ ገሰለሰቦች አርቲስቶች ሳይቀር ተገድለው ሀገር ለማፍረስ እርስ በርስ ለመጫረስ የተቻለውን ሁሉ ማድረግ ደረጃ ላይ ተደርሷል። ከኢትዮጵያዊነትም ከኦሮሞነት ወርደው አካባቢያዊነት እና ደምና አጥን ቆጠራ ከዛም ብሄርና ማንነት መካካድንና መንሳትን የፖለቲካ መቀስቀሻ አድርገው የሚሄዱበት፣ 7 ሺ የኦሮሞ ወጣት ተገብሮ ነው ይሄ ለውጥ ያመጣናው እንዳልተባለ ዳግም 7ሺ ወጣቶችን የጨረሰውን ስብስብ ወደ ስልጣን ለመመለስ የገዛ
417 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 08:09:14
344 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 21:26:49 የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን መሰረታዊ ጠላት ፥ ሌላ ሀይማኖታዊ ፍልስፍና ሳይሆን ፥ የንኡስ-ብሄርተኛ/ዘረኛ እሳቤ ነው። ከሌሎቹ የሀይማኖት ድርጅቶች ጋር ቢያንስ መሰረታዊ በሆነው የሰው ልጆች አፈጣጠር ፣ በሀልወተ ፈጣሪ፣ በሰው መነሻና መድረሻ በሆነው ''አፈርነት'' ፣ ከሞት በዃላ ስለሚኖረው ህይወትና በሚጠብቀን ፍርድ ፣ በጽድቅና ኩነኔ በሚባሉ ኮንሰፕቶች ላይ እንስማማለን። በተጨማሪም ከአንዳንዶቹ ቤተ እምነቶች ጋር ቁጭ ብለን ሊያነጋግረን በሚችል የጋራ የሆነ የእምነት መጽሀፍ ያለን ፥ በግለሰባዊ እምነታችን መሰረት ወደመረጥነው መጓዝ የምንችልና ተመሳሳይ በሆነው ተፈጥሯዊ ነጻ ፈቃዳችን ላይ የተመሰረተ የተመሳሰለ አስተሳሰብም አለን።

ከብሄርተኝነት/ዘረኝነት አስተሳሰብ ጋር ግን ያለን መሰረታዊ ልዩነት ገና ከመነሻው ከስነ-ፍጥረት ይጀምራል። ብሄርተኝነት የሰው ልጆች መነሻ የሆነዎ አፈጠጣር ይክዳል አልያም ማወቅ አይፈልግም አሁን ካለበት አደረጃጀት አንጻር እንጂ። ብሄርተኝነት በማንኛውም መልኩ ሌላውን ጎድቶም ቢሆን ጨፍልቆ መዘለቅን ያስባል እንጂ በጽድቅ በኩነኔ ከሞት በዃላ ስለሚኖረው ህይወት ፈጽሞ አይጨነቅም፤ ይሄን እንዲረዳው በስሩ የተሰለፉትን ሁሉ ከየትኛውም ሀይማኖታዊ አደረጃጀቶች በማራቅ ሀይማኖት የለሽ Atheist እንዲሆኑ ያደርጋል። መነሻቸውና ጥያቄያቸው Diversity መስሎ የሚነሳው የብሄርተኝነት ሾፋሪዎች አንድን ማህበረሰብ ወጥ ወደሆነ ብሄርተኛነት ለመምራት በተቻለው መጠን Religious Assimilation ማካሄድ ፈጣኑ መንገዳቸው ነው። በሀይማኖት የተለያየን ማህበረሰብ በብሄርተኝነት ስም አንድ አድርጌዋለሁ ማለት ጊዚያዊ መንጋ ከማግኘት ያለፈ ዘላቂና የጠነከረ ብሄርተኝነትን በማህበረሰቡ ውስጥ መገንባት እንደማያስችላቸው በሚገባ ያውቁታል። ማህበረሰቡ በውስጡ ያለውን ሀይማኖታዊ ማንነቶች አስቀድሞም ብሄርተኝነት እንዲቆሞ ሌላ ጠላት ህዝብ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ሀይማኖቶችም በሌላ አስተሳሰባዊ ጠላትነት ተፈርጀው ይቀመጣሉ። ለብሄርተኝነት ''ከሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ፣ ወንድማችሁን እንደራሳችሁ አድርጋችሁ ውደዱ፣ በራሳችሁ ላይ ሊደረግ የማትፈልጉትን በሌላ ላይ አታድርጉ.... '' ወዘተ ክርስትናዊ ፍልስፍዎች ቀልዶች ሲሆኑ ፤ Survival of the fittest መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው መመሪያው ነው። በብሄርተኝነት ነጻ ፈቃድ፣ ግለሰባዊ ነጻነት፣ ከመንጋነት ወጥቶ ማሰብ በጠላትነት ያስፈርጃል ብሎሞ ያስወግራል።

በየትኛውም ቦታ፣ በየትኛውም የማህበረሰብ ክፍል የሚያቆጠቁጥ ዘረኝነት ለክርስትና/ኦርቶዶክሳዊነት ጠላት መሆኑ ቢያንስ ለሁላችንም በጊዜ ሃደት የተረዳ ሆኗል። በብዙ ገፊ በሚመስሉ ምክንያቶች ወይንም በብዙ መጎዳትን በሚያስረዱ Logical reasonings ማሳመን የሚጀመረው የብሄርተኝነት ፍልስፍና መጨረሻው ፈጣሪን መካድና ሀይማኖት የለሽነት ነው። ይህም ታላቁ ጥፋት ነው።
....
ማርያማዊት ሄኖክ
519 views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 21:26:46
461 views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ