ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ² ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ³ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። ⁴ በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ⁵ ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም። @marsilchannel 3.4K views08:28