Get Mystery Box with random crypto!

ወንጌሉን እንጀምራለን ' በመጀመሪያው ቃል ነበር ' ( ዮሐ ፩:፩) እዚህ ምዕራፍ ላይ ትንሽ | ማዕዶት ዘተዋሕዶ

ወንጌሉን እንጀምራለን

" በመጀመሪያው ቃል ነበር " ( ዮሐ ፩:፩)

እዚህ ምዕራፍ ላይ ትንሽ እንቆያለን መሰረታዊ ምዕራፍ ስለሆነ ጊዜ ወስደን በተቻለ አቅም ሳይበዛ እንማማራለን

#በመጀመሪያው - መጀመሪያ የሚለውን ቃል ስናይ መነሻ ያለው መጀመሪያ አለ ፤ መነሻ የሌለው መጀመሪያ አለ በሁለት ይከፈላል
= ጥንት የሌለው መጀመሪያ ( ዮሐ 1:1 )
=መነሻ ያለው መጀመሪያ ( ዘፍ 1:1)

“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።” (ዘፍጥረት 1፥1 )

ዮሐንስ ወንጌል ላይ ያለው መጀመሪያ መጀመሪያ የሌለው መጀመሪያ መሆኑን የምናውቀው በመጀመሪያው ቃል #ነበር ይላል ኦሪት ዘፍጥረት ላይ ያለው መጀመሪያ መነሻ ያለው መሆኑን የምናውቀው በመጀመሪያ ሰማይ እና ምድር #ተፈጠሩ ብሎ ይነሳል #ነበርና #ተፈጠሩ ትልቅ ልዩነት አለው።

ስለዚህ #በመጀመሪያው #የምትለው #ቃል #ጥንት #የሌለው #መጀመሪያ #መሆኑን #ያስረዳል።

ቀጣይ በመጀመሪያ ሳይሆን የሚለው በመጀመሪያው ነው ለምን #"ው" የምትለው ቃል ተጠቀመ ለምን ??? እንመለስበታለን