2022-08-25 21:55:46
ፍቅር» ምን እንደሆነ ያውቁ ኖሯል???
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ነቢዩ ﷺ ለባልደረባቸው ሰውባን ረዲየሏሁ ዐንሁ ምንድነው ፊትህን የቀየረው? ብለው
ሲጠይቁት «በሽታም ሆነ ህመምም የለብኝም፤ ግን አንቱን ሳላገኝ ስቀር ከባድ የሆነ
ብቸኝነት ይሰማኛል፤ አንቱን እስከማገኞዎ ድረስ» ማለቱ ነው።
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ አቡበከር አስ-ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዐንሁ ከነብዩ ጋር በሂጅራ ጉዟቸው ወደ ዋሻ ከመግባታቸው በፊት
«ወሏሂ ካንቱ በፊት ካልገባው በስተቀር አትገቡም፣ የሆነ ነገር ቢኖር እንኳ ካንተ በፊት
እኔን ይጉዳኝ» ማለታቸው ነው።
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ዐሊይ ኢብን አቢ-ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ በነቢዩ ﷺ ፋንታ በፍራሻቸው መተኛታቸው ነው፤
የመካ ካ+ፊ+ሮ+ች ነቢዩን ﷺ ለመግደል መስማማታቸውና በዛ ፍራሽ ላይ ሊሞቱ
እንደሚችል እያወቁ መተኛታቸው ነው።
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ቢላል አል-ሐበሺይ ረዲየሏሁ ዐንሁ ነቢዩ ﷺሲሞቱ የነቢዩ ﷺ ፍቅር መዲና
አላስቀምጥ ብሎት አዛን ማድረጉን መተዉና መዲናን ጥሎ መሄዱ ነው፤ ይህ ብቻም
ሳይሆን ነቢዩ ﷺ በህልሙ መጥተውበት ምንድነው እንዲህ መጥፋት? ለምን
አትዘይረንም? ሲሉት ገና ሌሊቱ እንደነጋ የነቢዩን ﷺ ቀብር ዚያራ ለማድረግ መጓዙ
ነው፤ ከዛም አዛን እንዲያደርግ ለምነውት ያን ጣፋጩን አዛን ሲያደርግ የመዲና ህዝብ
በሙሉ በእንባ መራጨቱ ነው። ነቢዩ ﷺ ከሞቱ በኃላ እንጂ እንደዛ አይነት እልቅሻ
አልታየም ተብሎ በታሪክ ኢስኪፃፍ ድረስ።
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ከበኒ ዲናር የሆነች ሴት ባሏ፣ አባቷና ወንድሟ ወደ «ኡሑድ» ዘመቻ ወጥተው ሳለ
ሙስሊሞች ከውግያው ሲመለሱ ሁሉም እንደሞቱ ሲነገራት «ነቢዩ:ﷺ እንዴት ሆኑ?
ብላ መጠየቋ ነው፤ ከዛም እሳቸው አልሞቱም ሲሏት እሳቸውን ካላየው ብላ ነቢዩን ﷺ ስታያቸው «ካንቱ በኃላ ያለ ሙሲባ ሁሉ ለኔ ገር ነው» ማለቷ ነው።
.
እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ዙበይር ረዲየሏሁ ዐንሁ የ15 አመት ወጣት ሆኖ የነቢዩን ﷺ መገደል የውሸት ወሬ ሲሰማ
የመካ መንገዶች ላይ ሰይፉን እየጎተተ መውጣቱ ነው።
.
#እውነተኛ_ፍቅር_ማለት፦
☞ ረቢዐተ ኢብን ከዕብን ረዲየሏሁ ዐንዩ ነቢዩ ﷺ ምንድነው ሓጃህ (ጉዳይህ) ሲሉት ካንቱ: ጋር
በጀነት ጓደኛ መሆን ነው ማለቱ ነው።
.
«አንድ ሰው ከሚወደው ሰው ጋር በቂያማ ይቀሰቀሳል» ማለቶን እናውቃለን፤
@እኔም_አንቱ
የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! እንወዳችኃለሁ በአባቴ፣ በእናቴ፣ በቤተሰቦቼ፣ በንብረቴና
በነፍሴ ፊዳ ልሁንሎት አንቱ የአሏህ መልክተኛ ﷺ
86 views18:55