2022-02-01 22:12:08
“ወንጌላችን በኃይልና በመንፈስ ቅዱስ በብዙ መረዳትም እንጂ በቃል ብቻ ወደ እናንተ አልመጣምና፤ በእናንተ ዘንድ ስለ እናንተ እንዴት እንደ ነበርን ታውቃላችሁ።”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 1፥5
ይህ ወንጌል ወደ ተሰሎንቄ የመጣው በ ሀይል ነበር። ወንጌል የሚያምኑትን ሰዎች ሁሉ የሚያድን የ እግዝአብሔር ሀይል ነው ሮሜ 1:16 እናው ወንጌል ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች የመጣው ከ መንፈስ ቅዱስ ነበር መንፈስ ቅዱስም በ ጳውሎስ ውስጥ ነበር ። ሰዎችም ወንጌልን አምነው ከተቀበሉ ቦሀላ መንፈስ ቅዱስ ይኖርባቸው ጀመር። ይህንንም ወንጌል መንፈስ ቅዱስ እንጂ ፊደል ሊገልጥል አይችልም ።
“እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።”
— 2ኛ ቆሮ 3፥6
ተሰሎንቄ የሰሜናዊ የግሪክ አውራጃና የመቄዶንያ ዋና ከተማ ነበረች። ይህንንም መልዕክት የፃፈው ተሰሎንቄን ከጎበኘ ከ ጢቅት ግዜ ቦሃላ ነበር በ ቆሮንቶስ በ 50 ዓ.ም የፃፈው ። ይህንንም እውነተኛውን የ እግዚአብሔርን ወንጌል አምነው የተቀበሉ አማኞች ነበሩና በሰዓቱ በነበሩ ነገስታት ከፍተኛ የሆነ ስቃይ ይደርስባቸው ነበር ይህንንም መልዕክት ስጽፍላቸው በ ተሰሎንቄ ያሉትን አዳዲስ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት ነው ።
ዛሬም የ እግዚአብሔር ቃል ህያው ነው ። ወዳጆቼ ይህ የ እግዚአብሔር ወንጌል ተገልጦልናል ያበራልንም መንፈስ ቅዱስ ነው እናም ድካማችንን የምያግዝ መንፈስ ቅዱስ ስላለ በ ኢየሱስ ክርስቶስ አምነን የዘላለምን ህይወት አግተናልና እንግዲህ እንጽና ።
በክርስቶስ ኢየሱስ በያዝነው እውነትም እንበርታ ።
“የጌታ ቃል ግን ለዘላለም ይኖራል። በወንጌልም የተሰበከላችሁ ቃል ይህ ነው።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 1፥25
መልካም ቀን
@lzemrlegeta
@lzemrlegeta
@lzemrlegeta
Share
Share
85 viewsℓιnυ azusa revival , edited 19:12