Get Mystery Box with random crypto!

የጸሐፊው ሀደራ ከድንቅ ኢትዮጵያውያን (ከወንድሞቻችንና ከእህቶቻችን) የደም ጅረት የተቀዳን የመስዋ | Life Wisdoms College📚

የጸሐፊው ሀደራ
ከድንቅ ኢትዮጵያውያን (ከወንድሞቻችንና ከእህቶቻችን) የደም ጅረት የተቀዳን የመስዋዕትነት ደም ፍሬ እና ከአጥንታቸው ተፈልጠን ፣ ከሥጋቸውም ተቆርሰን በተዋችው ነፍሳቸው ነፍስ የዘራን የወጣት ጉብሎቻችን እና የሽማግሌ አባቶቻችን ተወካዮችና ሀደራቸው የተጣለብን መሆናችንን አንርሳ።

በዱር በገደሉ ያልደከመው ጉልበታቸው ፣ በቁር በሀሩሩ ያልዛለው ኢትዮጵያዊነታቸው ፣ እንደ ውኃ የፈሰሰው ደማቸው ፣ እንደ እንጨት የደረቀው አጥንታቸውና በቁራና በአውሬ የተቆረሰው ሥጋቸው ለእኛና ለእኛ ብቻ ነው። ስለዚህ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ቢመቸንም ባይመቸንም ባለንበት ሥፍራ ሆነን ለእናታችን ለኢትዮጵያ በግብ ሕይወት ለመኖር እንትጋ።
:
:
:

Touch it & then Join it!

https://t.me/LifeCollege
https://t.me/LifeCollege