#አስቸኳይ_ማሳሰቢያ ለ2014 የትም/ት ዘመን 12ኛ ክፍል ማጠቃለያ (ሀገር አቀፍ ) ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ በ2014 ዓ.ም የመደበኛም ይሁን የግል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና ምዝገባ ሂደት በሁለት(በዳርማሎግ/online/ እና በ"DRS"/በወረቀት) አማራጮች እየመዘገብን መቆየታችን ይታወሳል። ሆኖም ግን ጥቂት ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች የአንደኛውን አማራጭ ምዝገባ ብቻ በመመዝገብ ቀሪውን እንደዘለሉት ከመዋቅሮች የሚመጡ መረጃዎች ያሳያሉ ፤ ስለሆነም ማንኛውም ተማሪ የ2014 12ኛ ክፍል ፈተና መፈተን የሚችለው ሁለቱንም የምዝገባ አማራጮችን አሟልቶ ሲጠቀም ብቻ እነደሆነ በአፅንኦት እየገለፅን ፤ የDRS ምዝገባ ያልተመዘገባችሁ በሙሉ ቀሪ ሁለት ቀናትን (ከሀምሌ 04 እስከ 05/11/2014) በመጠቀም ቀደም ስል በተመዘገባችሁበት ትምህርት ቤት በአካል በመቅረብ አሰፈላጊውን እንድታሟሉ እናሳስባለን። ትምህርት ሚኒስቴር @kokebe_tsibah_meme 1.7K views20:15