በሀገራችን፡ፍትህ፡ስደተኛ፡ናት። ከሰው፡ልብ፡ሸሽታ በገዥዎች፡ሸንጎ ጥገኝነት፡የምትጠይቅ ደጅ፡ጠኝ፡ሆናለች። ራስ፡ወዳድነት፣አስመሳይነት፡እና ስስት፡ተበራክተው፡ፍትህን፡አደቀቋት፤ ደበደቧት። መውጫ፡መግቢያ፡ነሷት። ሸሸች። ከሰው፡ልብ፡ጠፋች። ከሜዳ፡ሜዳ፡ስትዞር ከመንግስት፡ስር፡መጠጊያ፡አገኘች። መንግስት፡ደግሞ እንደማንኛውም፡ስደተኛ ንብረቱ፡አደረጋት፡፡ ሲያሻው፡ሰጥቶ ሲያሻው፡የሚነፍጋት፡ሆነች። ሰው፡ከልቡ፡ያለውን፡ፍትህ፡አባርሮ መንግስትን፡መልሰህ፡ስጠኝ፡ቢል ከየት፡ይሰጠዋል? ዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ @kene_tobeya 835 views ⓐⓜⓐⓝ, 21:00