Get Mystery Box with random crypto!

ኬልቅያስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ keleotc — ኬልቅያስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ keleotc — ኬልቅያስ
የሰርጥ አድራሻ: @keleotc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 360
የሰርጥ መግለጫ

ኬልቅያስ የቴሌ ግራም ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የነፍስ ማዕዶችን የሕይወት ቃል ወንጌለ መንግሥት የምስል ( vidio ) ትምህርቶች ፣ ያሬዳዊ መዝሙራትን ፣ የቅዱሳን ዜና ሕይወት ፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ የአብያተ ክርስቲያናት እና የገዳማት ታሪክ ፣ የአባቶች ምክር ፣ የጠቢባን የአባቶች አባባል ፣ መንፈሳዊ ጥቅሶች እና ኪነ - ጥበባዊ ልዩ ልዩ አውዶች የሚቀርብበት ነው።

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-23 09:35:13 I ህቡዕ ገጽ
ህቡዕ ገጽ
ህቡዕ ገጽ

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ
ክፍል ሁለት

2008 ዓ.ም ባሌ ጎባ
እሁድ ምሽት 1:30

የተሰበሰበው ሰው የሚሆነውን ሲጠባበቅ ሁለት ሕግ አስከባሪዎች እየሮጡ መተው ያለማቋረጥ አንዱ ይደበድበው ጀመር። ዱላው ሲጀመር ውሱን ሰዎች " ኧረ እብድ ነው ተውት" የሚል ድምጽ ቢያሰሙም እምብዛው ግን " ልብሱን አስወልቆ ነው ኢሄንን መግረፍ ምን እብድ ነው? አውቆ አበድ አስመሳይ።" ሲሉ ዱላውን በዝምታ ሲቀበል ቆይቶ በፓሊስ ዱላ ዓይኑ አካባቢ በተመታው ከባድ ምት መቆም ተስኖት ሰማይ ምድሩ ዞሮበት ወደቀ።

ህመሙን ተቋቁሞ ያለውን ኃይል ሁሉ ተጠቅሞ ተነስቶ ሲቆም አንድ ዓይኑ ተጋርዳለች። እንደምንም ሲመለከት ፖሊሶቹ ትተውት እየሄዱ ነው። ከቆመው ሕዝብ ጀረባ ስትጮህ የመጣችውን ልጅ ከበዋት ያረጓጋታል። ይህን ሁሉ ቆሞ ሲመለከት ከነዓን ነገሩ ግራ አጋብቶታል። ፍጻሜውን ለማየት እንደቆመ ተደብዳቢው ሰው "" ፍትህ ጎድሏል ሞት ተፈርዷል ነፍስ ታደጉ" እያለ መጮህ ሲጀምር ሕግ አስከባሪዎቹ ተመለሱ። " ኡሌ ሂን ቁፍኔ?" አለው አንዱ ደብዳቢው ከሁለቱ። "" ሕይወት አድኑ ነፍስ ታደጉ"" አለ ተደብዳቢው በድጋሚ። ከተመለሱት ቀድሞ ሲደበድበው የነበረው ተንደርድሮ ኩላሊቱን በከስክስ ቢረግጠው የኋሊት ሲወድቅ ጭንቅላቱን ድንጋይ አጊኝቶት ደሙ ይንቆረቆር ጀመር። ዳግም ተነስቶ ደሙ ፊቱን እያጠበው " የእግዚአብሔርን መቅደስ ቤትሽን ሰውነትሽን የምትወጂ ሌላውን መቅደስ እንዲፈርስ በጭካኔ ለተሞላሽ ላንቺ ፍርድ ይገባል።" እያለ ሰዎች ወደ ከበቧት ሴት መጠቆም ጀመረ።

ገሚሱ ሰው ነገሩ አልገባ ስላለው ትቶ ሄዷል። በዚ መሀል ነበር የኔታ ጀምበሩ ከዋሉበት ወደቤት እያቀኑ ተሰብሳቢውን ሰው ሲያዩ "" ሰአሊለነ ቅድስት"" ሲሉ ከነዓን ሰምቶ "አይዞት የኔታ ቀላል ነገር ነው" በማለት ምላሽ ሲሰጥ "ለመሆኑ ምንድነው?" በማለት ጥያቄ ሲሰነዝሩ " አንድ እብድ..."" ሳይጨርስ " ምን ሆነ ዝምተኛው?" አሉት የኔታ። አንዲት ሴት አባሮ ሰው ደርሶ ታደጋት ክፉ አላደረሰባትም። እንዲያውም እርሱ ነው በፖሊሶች ዱላ ቲኒሽ የተጎዳው።" ሲላቸው ደነገጡ። የኔታ ከዚ በላይ መታገስ አልወደዱም በህዝቡ መሀል አልፈው አንድ ዓይኑ ተራራ ያከለ የሚጮህ ሰውጋ ደርሰው "" ምን ገጠመህ ዝምተኛው?" አሉት።

ሕግ አስከባሪው "" ኢሲን ሩኩታ ኢቲሂንሲቂና" ሲል ከጎናቸው ያለ ከነዓንን ""ምንድነው የሚለው"" አሉት። " እንዳይመታዎት ነው የሚለው እርሶ ተጠንቀቁ"" አለ እርሱም አክሎ። የሚፈሰውን ደም ያበጠውን ዓይኑን አይተው የኔታ በስሜት "" የማታስተውል መምህርህን የምትደበድብ ተማሪ"" ብለው ሲጮሁ ሰው ሁሉ ትኩረቱ ወደረሳቸው ሆነ። "" ማነው ያበደ እርሱ ወይ እኔ ወይ እናንተ?" ሲሉ ሕግ አስከባሪዎቹ እሳቸውንም ለመምታት ዳዳቸው። ነገር ግን የሃይማኖት አባት መሆናቸው ሌላ ችግር እንዳይፈጥር ተው።

"" አንቺ ምን ስልጣን ኖሮሽ ነፍስ ላይ ሞት የምትፈርጂ"" አለ ደሙ እየተንጠባጠበ። " ሰው ባያይ አምላክሽ ሁሉን እንዲያይ አይምሮሽ ስለምን ዘነጋ?"" አለ ደግሞ። "" ማናት?"" አሉ የኔታ። "" እርሷ"" አለ አጠገቧ ደርሶ። "" ድረሱላት እርሷ ማህጸኗን ረግማለች ራሷን እኔ አይደለሁም ብላ ክዳለች ድረሱላት"" እያለ ደሙን እያዘራ ወደመጣበት እያነከሰ ይሮጥ ጀመር።

የኔታ ወደ ወጣቷ ተመግተው " ምን አጥፍተሻል ልጄ?" ሲሏት መንቀጥቀጥ ጀመረች። "አይዞሽ አሁን እረሰሱም ሄዷል አትፍሪ ንገሪን?" አሏት በተማጽኖ። " አፍ የለኝም አላወራም ጥፋቴን በጥፋት ሳርም ጥፋት የገጠመኝ ባይተዋር ምስኪን ሰው ነኝ። ሕመሜን ያልፋል ብዬ እሹሩሩ እያልኩ ሳላውቅ አሳደኩት ዛሬም ከወገቤ አልወርድ አለ። አልችልም በቃ አሁን አልችልም"" ብላ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። የነበረው ሰው ተደናገጠ። "" አንዷ ወጣት ምንድነው ግርግሩ?" ብላ ስትጠጋ ባየችው ነገር ተደናገጠች። "" ራሄል "" አለች ጮክ ብላ። " ምንሆንሽ ምን ገጠመሽ?" የኔታ ቀጥለው "" እስቲ ሁላችሁም ወዲያ ሂዱ ብቻዋን ላውራት" ሲሉ ከጥቂት ሰዎች ውጪ ሌላው ወደየመንገዱ አቀና። የኔታና የምታውቃት ማርታ ብቻ ከአጠገቧ ሲቀሩ ከነዓን ርቆ ቆሟል። ዝምታ ሰፈነ በድንገት ራሄል " አባቴ ነፈሰ ገዳይ ነኝ ልጄን የጣልኩ ጨካኝ" ስትል " እመብርሃን ድረሽ" አሉ የኔታ። " ከንድ ችፍግ ስር አስቀምጬው ስዞር እብዱ አየኝ ተከተለኝ ስሮጥ ከኋላዬ እየሮጠ ተመለሽ ክህደት ነው። ሲለኝ ጮህኩ ሰዎች ደርሰው ይኼ ሁሉ ሆነ። በኔ ምክንያት በበደሌ ለኔ የሚገባውን እብዱ ተቀበለ ሲደበድቡት እንኳን ተውት ለማለት ከእውነት ፍረሀት አሸነፈኝ።" አለች ራሄል።

የኔታ "ልጄ ነገሩ ጊዜ የሚሰጠው አይደለም አንቺ ከዚህ ልጅ ጋር ወደቤት ሂጂ። እኔና ጓደኛሽ ቶሎ ብለን ሄደን ለልጅሽ ልንደርስለት ይገባል።" ብለው ከነዓንን ጠሩትና " እባክህን ወደቤቷ አድርሳት ብለው እየተቻኮሉ ከማርታ ጋር እብዱ ወደሮጠበት አቀኑ። የኔታ እብዱ የምን ጊዜው መገኛው እግር የማይበዛባት በተለየም ማታ ሰው የማይሄድባት ጎዳና ላይ መነኛውን ስለሚያውቁ ወደዚያው አቀኑ። ቦታው ላይ ሲደረሱ የኔታና ማርታ ባዩት ነገር አንባቸውን መቆጣጠር አቃታቸውና ቆመው አለቀሱ። እብዱ ደሙ እየፈሰሰ እሳት አንድዶ የሚለብሰውን ዲሪቶ አንጥፎ ሕፃኑን አስተኝቶ ከላይ እናቱ አልብሳ የጣለችውን ኩታ አልብሶት እርቃኑን ቁጭ ብሎ ያለቅሳል። የኔታ እንባቸውን እየጠራረጉ ተጠግተው " ዝምተኛው ዋጋህን እማምላክ ትክፈልህ ስለኛም አብዝተህ ጸልይ ስራህ ታላቅ ነው። እንካ ይሄን ልበስ" ብለው የኔታ የለበሱትን ካቦርት ሰጡት። ሕፃኑንም ወስደው ማርታ ታቅፋው ወደቤት አቀኑ። ቤት እንደደረሱ ከነዓን አጠገቧ ተቀምጦ ራሄልን ስታለቅስ አገኟት። "በይ አሁን ለቅሶሽን አቁሚ ይኸው ልጅሽ" አሏት የኔታ። ከማርታ ልጁን እያለቀሰች ተቀብላ አቀፈችው። "ቆይ ለመሆኑ የምልሽ ልጄ ዘንግቼው አባቱ ልጁን ለማሳደግ ፈቃደኛ አይደለም?" አሏት። " መቼ ልጁ መሆኑን አምኖ" አለች ራሄል። "" አንቺ ታውቂዋለሽ አይደል?" አሉና የኔታ አብራው የተኛችውን ሰው እንዴት አታውቀውም ምን ማለቴ ነው ብለው በራሳቸው ሲገረሙ " እንኳን እኔ እርሶም እሱም እሷም ታውቁታላችሁ" ብላ ወደ እያንዳንዳቸው ስታመለክት ሁሉም ደነገጡ። " ማነው እርሱ?" የኔታ ጠየቁ። ራሄል እያለቀሰች አንዴ በስስት ልጇን እያየች ሳግ እያነቃት "" አ...ባ ወል...ደ...."" ስትል የኔታ አቋርጠዋት "" የልጁን አባት እኮ ነው የምልሽ "አሏት ደንግጠው።

""አዎ እኔም የምነግሮት ቆቡን ስላላከበረ ዓለምን ካድኳት ብሎ ዓለምን ተሸክሟት ስለሚዞር እድሌን ስለሰበረ ልጄን አይደለም ምንኩስናውን ስለካደ ስለዚህ ሕፃን አባት ነው የምነግሮት።" አለች ቃላቶቿ ወላፈኑ እንደሚያቃጥል ነበልባል እየተንቦገቦገ። " ልጁ አባቱ መነኩሴ ናቸው ነው የምትይኝ?" አሉ የኔታ ደንግጠው ስሙን ለመስማት አቅም እያነሳቸው። " አዎ" አለች እያለቀሰች "" አባቱ አባ ወ...ል.....ደ........

ይቀጥላል
ሐምሌ 16/2014 ዓም
301 viewsናትናኤል ጎሳ, edited  06:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 10:17:24 በሬን ላልከፈትኩለት ድንግል ሆይ አሳስቢ
ቅድስት ሆይ ለምኝልኝ

ድንግል ሆይ አንቺ የቤቴ በረከት ነሽ። ልጅሽም የነፍሴ እረፍት ነው። ንዒ በሚል ዝማሬ አንቺን እጠራሻለሁ።

እርግጥ ነው ልጅሽን ይዘሽ ወደኔ ስትመጪ እንደ ቤተልሔም የእንግዶች ማረፊያ የኔም ልብ የብዙ እንግዳ ኃጢአቶች ማደሪያ ነውና ልጅሽን ለማስተኛት ቦታ የለኝም ብዬ የልቤን በር ልዘጋብሽ እችላለሁ።

በሩን ብዘጋውም ግን ልጅሽ ከደጅ ቆሞ "በሩን ማንኳኳት" እንደማይሰለቸው አውቃለሁ። ራዕ 3:20 እኔ ፈቅጄ ባልከፍትለትም እንኳን የድንግልናሽን ማኅተም ሳይከፍት እነደተወለደ የእኔንም የተዘጋ ልብ ሳይከፍት መግባት አይሳነውም።

ስለዚህ አመፄና እንቢታዬን ቸል ብለሽ ለልጅሽ ማደሪያ አድርጊኝ። አንቺ እርሱን ከወለድሽ ወዲያ በታተመ ድንግልናሽ ጸንተሽ እንደኖርሽ ለልጅሽ ማደሪያ ሆኜ ለሌላ የኃጢአት ጽንስ ዳግም ማደሪያ አንዳልሆን ነፍሴን አትሚልኝ።

ድንግል ሆይ አንቺን ያሳደደሽ ሔሮድስ እኔን የማያሳድደኝ ልጅሽ በእቅፌ ስለሌለ ነው። እኔ በልቤ ያነገሥኩት " የተወለደውን የአይሁድ ንጉሥ" አይደለምና ከሔሮድስ ምንም ጠብ የለኝም። አሁን ግን ፍቀጂልኝና ሔሮድስን ማስደሰት ትቼ ልጅሽን በልቤ ልቀበለው።

በሬን ለዘጋሁት ለእኔ እናቴ ሆይ ልጅሽን በሬን ሲያንኳኳ ሳልከፍት እስካሁን ለዘገየሁት የንጉሡ እናት ሆይ አሳስቢልኝ።

ቅድስት ሆይ ለምኚልኝ
338 viewsናትናኤል ጎሳ, 07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 10:17:17
173 viewsናትናኤል ጎሳ, 07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 22:30:47
240 viewsናትናኤል ጎሳ, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 22:30:31 እውነተኛ ታሪክን መሰረት ያደረገ ልብ አንጠልጣይ
"" ህቡዕ ገጽን""
በኬልቅያስ የቴሌግራም channel ዘወትር ሰኞ፣ረቡዕ፣ቅዳሜ ይከታተሉ።
233 viewsናትናኤል ጎሳ, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 12:15:49 ህቡዕ ገጽ
ህቡዕ ገጽ
ህቡዕ ገጽ

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ
ክፍል አንድ

ፀሐይ በደመና ተጋርዳ ሰማዩ ጥላ አጥሏል። አየሩ ነፋሻማ ምቹ ስለነበር ህዝቡ ከፊታቸው በእንባ እየታጠበ የሚሰብከውን ሰባኬ ወንጌል ጸጥ ረጭ ብሎ ያደምጠዋል። ሕፃናት ሳይቀሩ በመምህሩና ከሕዝብ መካከል በሲቃ እየታፈኑ ከሚያነቡት ከብዙዎቹ ማንባት ምን መጣ በሚል ተደናግጠው ተቀምጠው ሰባኪውን ዓይን ዓይኑን ያያሉ።

""" ኢካቦድ""" ክብር ከእስራኤል ለቀቀ። ቀደምት የስልጣኔ ምድር የጥበብ አሻራ የቅዱሳን ምድር የድንግል አስራት ሀገረ እግዚአብሔር ኢት.....ሳግ አነቀው.....ዮጵያ""ፊደላቱን አምጦ ወለዳቸው።
""""ዛሬ ለምንድነው የጦርነት ምድር የደም መሬት የሆነችው?
እንግዳን ተቀባይ የነበረች ምን ነክቷት ነው ልጆቿን ረሀብ የሚቀጣቸው?
ለምንድነው ወንድም በወንድሙ ጨክኖ ሾተል የሚስለው? ቃታ የሚስበው?
ለምንድነው ክርስቲያኖች የመከራ ሽልማት እጩዎች የሆኑት?""""

ጉባኤው ሆድ ባሰው ህዝቡ የገረፉት ሕፃን ይመስል እየተንሰቀሰቀ በለቅሶ እንባ ፊቱን ያጥባል። ሰባኪው በዓይኑ እየቃኘ በእንባ አይኖቹ ፍም መስለው ቀጠለ። አሻግሮ ሲመለከት እርምጃቸው የተለየ ሁለት ሰዎች ከውጭ ሲገቡ አየ። ሰዎቹ ከአንድ ትልቅ አጸድ ስር ሳይሳለሙ ተደግፈው ቆሙ። ስብከቱ ቀጠለ።
""" ኑ እናልቅስ ኑ እንመለስ ኑ ወደቤታችን እንግባ ኑ እናንባ አንተ ሰበርከን ኑ አንተ ጠግነን እንበል። ኑ በንሰሐ ዳግም እርቅ እንፍጠር። ኑ ሀገር እናንሳ ኑ ሀገር እንሁን ኑ ፍቅርን እናንግሥ ኑ ጥላቻን እንቅበር።""

አንዳንድ አረጋውያን በነጠላቸው እንባቸውን ጠረገው ቀና ሲሉ ሲያይ ሰባኪው የእንባው ጅረት ይጨምራል። እንዲያም እያነባ ቀጥሏል። ወደ መግቢያው የውጭ በር ሲያይ አንድ ትጥቅ የታጠቀ የፖሊስ ልብስ የለበሰ ሰው ስልክ እያወራ ገብቶ አጸዱን ተደግፈው ከቆሙ ሁለት ሰዎች ጋረ ሰላምታ ተለዋውጦ ቆመ።
"" ሰባኪው ዛሬ አስቦ ወደመድረኩ የወጣው ሌላ ርዕስ ነበር። አሁን የሚሰብከው ርዕሱም ያላሰበው ስለነበር የሚናገራቸው ቃላቶች ሁሉ ከሌላ እንዲሰማው ሆነው እየተሰሙት ልቡ ተነክቶ እንባው ገደብ አቷል። "" የእግዚአብሔር ቤተሰዎች"" አለ ሰባኪው። "" በእኛ የሆነው እርግጥ ከባድ ነው።""

ሰቆ ኤር 5:16-17 እንዲህ ይላል"" አክሊል ከራሳችን ወድቆአል ኃጢአት ሰርተናልና ወዮልን! ስለዚህ ልባችን ታምሞአል ስለዚህም ነገር ዓይናችን ፈዞአል።""" ከመጽሐፍ ቃሉ ሲነበብ ለካ ጉዳችን ከዚህ ተጽፏል በሚል ለቅሶው ከሕዝቡ ቀጠለ። ሰባኪው በቃለ ተማጽኖ ትምህርቱን አጠናቆ ተቀመጠ።

ቀጣይ "ማረን አባታችን" የሚል የንሰሀ ዝማሬ ጥኡም በሆነ ለዛ ባላት አንዲት ዝማሬ ቀርቦ ሌሎችም ዝማሬዎች ተዘምረው በጸሎት ጉባኤው ተጠናቀቀ።

ሰባኪው ከነበሩት አባቶች በእድሜ ከገፉት ተባርኮ ተሰናብቶ ሲሄድ አንድ ፀጉሩ የተንጨባረረ ወጣት "መምህር" ሲል ሰባኪው ቆመ። " ይቅርታ!! አንተ እያልኩ ባወራህ...."" ሲል "" ችግር የለውም" አለው። ወጣቱ ""ስሜ ከነዓን ይባላል"" ብሎ እጁን ሲዘረጋ ሰባኪው " ንፍታሌም" ብሎ ጨበጠው። " መምህር የማወራህ ምሥጢር እና ጥቂት ጥያቄ ነበረኝ" ሲል ተሰናብቶ የሚሄደውን ሕዝብ አቋርጣ አንዲት ቆንጆ ልጅ "" አሁን የሰበከውን መምህር ሊያስሩት ነው። ብዙ ፖሊሶች ደጅ ቆመዋል መኪናቸውም ደጅ ቆማለች አጸዱ ጋር የቆሙት ሶስት ሰዎች ሲዝቱ ሰምቻለው።"" እያለች ድምጿን አሰምታ እየተዋከበች ሰባኪው ጋር ደርሳ "" አምልጥ ከጀርባ ውጣ ይገድሉሀል"" ስትለው እየወጣ የነበረው ሰው ሁሉ ከጥቂቶች በቀር ወደ ኋላው ተመለሰ።
"" እኛን ሳይገድሉ አይዙት መቼም" አሉ መቋሚያ የያዙ አንድ አዛውንት። ሌላውም ሰው ሁሉም እርስበርስ እያጉረመረመ ሌላው ጥግ ይዞ ግማሹ ወደ ሰባኪው ሲያቀና ከአጸዱ ስር የነበሩ ሶስት ሰዎች ሰባኪው ወዳለበት መራመድ ጀመሩ። ከውጭ ያሉ በርካታ ፖሊሶችም ወደ መግቢያው በር ተጠጉ።
"" አይዞሽ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው ይጠብቀኛል።" ብሎ ይሸሻል ብላ የጠበቀችውን ቆንጆ ልጅ ትከሻዋን ቸብቸብ አደረገና ወደረሱ ወደሚመጡት ሶስት ሰዎች መራመድ ጀመረ። ከሶስቱ አንዱ ትጥቅ የታጠቀው "ሌሎቻችሁ ሂዱ ግቡ" ሲል አንድ የሰማይ ስባሪ የሚያህል የፈረጠመ ወጣት ሶስቱ ሰዎች ፊት ቆሞ "ከመምህራችን ፊት ሞታችን ይቅደም ኢኸው ግደሉኝ።" ሲል ሌሎችም ተከታትለው ፊታቸው ቆሙ።

ሰባኪው አጠገባቸው ደረሶ "ማንን ትፈልጋላችሁ?"" ሲል መቋሚያ የየያዙት ትልቅ አዛውን "እኔ ልሙት ልጄን ምን ባጠፋ?" አሉ እያለቀሱ። "ለጥያቄ ጣቢያ ፈልገን ነው እባክህን ሌሎችም ባልደረቦቻችን መኪና ይዘው እየጠበቁን ነው። መምህር ማነው ስምህ ?" አለ ሌላው ከሶስቱ። ከውጭ ሆነው ለሁለት ተከፍለው ሲከራከሩ ከነበሩት ገሚሶቹ ህግ አስከባሪዎች ወደ ቤተክርስያኑ ግቢ ገብተው ወደ ተሰባሰበው ሰው አቀኑ።
2014 - ሐምሌ- ሐሙስ
ክፍል ሁለት ይቀጥላል
396 viewsናትናኤል ጎሳ, edited  09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 15:42:23
48 viewsናትናኤል ጎሳ, 12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 15:29:46 ታቅፌው እንድውል ፍቀጂልኝ
ታቅፌው እንድውል ፍቀጂልኝ

ድንግል ሆይ ወዳንቺ መጥቶ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ ያለሽ መልአክ ዛሬም ወደኔ ይምጣ።

ኃጢአት ያደቀቃት በኀዘን የተዋጠች ነፍሴን ከጸጋ የተራቆትሽ ሆይ ደስ ይበልሽ ይበላት። ጌታ በእኔ ልብ እንዳይፀነስ ያለ ኃጢአት መኖርን ስለማላውቅ እንዴት ይሆንልኛል? ብልም ወደ አንቺ የመጣው መንፈስ ቅዱስ ወደ እኔ በምህረት ይምጣ።

በእስራኤል ልጆች ሠፈር መና እንደወረደ የልጅሽ ምህረት በእኔ ላይ ይውረድ። የኃጢአት አሳብ ከልቤ አውጥተሽ በሕሊናዬ ልጅሽ እንዲያድር ለምኚልኝ።

ጌታን በእጆችሽ መሃል የያዝሽው ሆይ አንቺ ጌታን ለዓመታት ታቅፈሽው ነበር። እኔ ግን ለአንድ ቀን እንኳን ሰውነቴ ከኃጢአት አርፎ እርሱን ብቻ ታቅፌ እንድውል ፍቀጅልኝ።

!! አሜን !!
49 viewsናትናኤል ጎሳ, 12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 22:39:33
47 viewsናትናኤል ጎሳ, 19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 15:03:19
48 viewsናትናኤል ጎሳ, 12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ