Get Mystery Box with random crypto!

††† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ኩትን ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† | ✞ገድለ ቅዱሳን✞

††† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ኩትን ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ሐዋርያው ቅዱስ ኩትን †††

††† ቅዱስ ኩትን በዘመነ ሐዋርያት የነበረ: ከአሕዛብ ወደ ክርስትና በቅዱስ ዻውሎስ አማካኝነት የተመለሰ: ከቅዱሳን ሐዋርያት እግር ሥር ቁጭ ብሎ ይማር ዘንድ የታደለ: በፍፁም ድንግልናው የተመሰገነ ሐዋርያዊ አባት ነው::

ይህ ቅዱስ ሚስት ነበረችው:: ግን በትዳር ውስጥ ሆኖ ድንግልናን መጠበቅ እንደሚቻል ያሳየ የሐዲስ ኪዳን ሰው ነው:: ቅዱስ ኩትን በንጽሕናው: በአገልግሎቱና በጣዕመ ስብከቱ በሐዋርያትና ምዕመናንም ተወዳጅ ነበር:: ለብዙ ዘመናት በወንጌል አገልግሎት ኑሮ በዚሕች ቀን በመልካም ሽምግልና አርፏል::

††† ፈጣሪ ከበረከቱ ያድለን::

††† መጋቢት 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ኩትን ሐዋርያ
2.ቅዱስ እንድርያኖስ ሰማዕት
3.ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት
4."2,000" ሰማዕታት (የአባ ኖብ ማሕበር)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት)
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ኢትዮዽያዊ)
3."318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት (ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ)
4.የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
5.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ (ኢትዮዽያዊ)
6.ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ (ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት)

††† ". . . ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር የወደደውን ያድርግ:: ቢያገባም ኃጢአት የለበትም:: ሳይናወጥ በልቡ የጸና ግን ግድ የለበትም:: የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል:: ድንግልናውንም በልቡ ይጠብቅ ዘንድ ቢጸና መልካም አደረገ:: እንዲሁም ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ:: ያላገባም የተሻለ አደረገ::" †††
(1ቆሮ. 7:36-38)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††