Get Mystery Box with random crypto!

1.ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጉዋታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹ | ✞ገድለ ቅዱሳን✞

1.ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ
አሳርጉዋታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹም
ተሸክሞ: አስቅድሞ
ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል:: በዚህም
ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ:
የምትለምንና የምትማልድ
ሆናለች:: ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን
ተቀብላለች::
2.ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ
ኢትዮዽያ መርቶ አምጥቷታል:: በክንፉ ተሸክሞ: በ4
አቅጣጫ አዙሮ
አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጉዋል::
3.ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ
በኢትዮዽያ ወንዞች ላይ አፍስሷል::
4.ለብዙ ቅዱሳን (አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ) ጽዋዐ ልቡናን
አጠጥቷል::

✞አምላከ ቅዱሳን ስለ ወዳጆቹ በጐ ምኞታችንን
ይፈጽምልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

✞ጥር 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=

1.ቅዱስ አባ እንጦንስ (የመነኮሳት አባት-የበርሐው
ኮከብ /ልደቱና ዕረፍቱ)
2.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላዕክት (ለተጠሙ ጽዋዓ
ልቡናን የሚያጠጣ: ምሥጢር ገላጭ መልዐክ)
3.ቅዱስ ሚናስ ኤዺስ ቆዾስ

ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
3.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ)
4.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
5.አባ ዻውሊ የዋህ

++"+ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ::
መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ:: ነፍሱን ሊያድን የሚወድ
ሁሉ
ያጠፋታል:: ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ
ያገኛታል:: +"+ (ማቴ. 16:24)

✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር