2022-04-22 10:55:14
ከምንወዳት እና ከምናከብራት መዓዛ ብሩ ጋር የነበርኝን ጨዋታ ነገ ቅዳሜ ከቀኑ 9 ሠዓት እስከ 11 ሠዓት በሸገር FM 102.1 ላይ አብረን ብናደምጥ ምን ይመስላችኋል?
——————————————————————
በዚህ ሳምንት በጨዋታ እንግዳነት የምናቀርበው ወጣት ሙዚቀኛ እስከዛሬ ከቀረቡት እንግዶች ወጣቱ ነው፡፡
በእድሜ አንጋፋነት ሬከርዱን የያዙት በ110 ዓመታቸው ያገኛናቸው የፊታውራሪ ሃብተጊዮርጊስ ባለሟል የወሊሶው ቀኝአዝማች አስፋው ነበሩ፡፡
ዛሬ ልዩ የአውዳመት እንግዳ አድርገን ያቀረብነው በመድረክ ስሙ ካሥማሠ ወላጆቹ ባወጡለት ስም ፍቅሩ ሠማ ሰዓሊና ሙዚቀኛ ነው፡፡
የዛሬ ዓመት ግድም ማለዳ የተሰኘ አልበም ከዓመት በኋላ ሁለተኛ አልበሙን ካሥማሠ ባህል ወግ አቅርቧል፡፡
የካሥማሠ ሙዚቃ ዘይቤ (ለኔ አንደሚሰማኝ) ብዙዎችንም ይሰማ ይመስለኛል ከእኛ ጋር የተዋሃደው የኢትዮጵያ ሙዚቃ ዘይቤና የለመደውና ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ስልት አዲስ የሆነው ስልት ውህድ ነው፡፡
እሱ አንጻር ይለዋል ይሄን አዲስ ዘይቤ
ፍቅሩ ሠማ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዲግሪውን በ2009 ዓ.ም በንግድ ስራ ኮሌጅ (በMarketing) አግኝቷል፡፡
ቅዳሜ ሚያዝያ 15 ከቀኑ 9 በሰዓት በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ይከታተሉ።
#MeazaBirru #kassmasse #Chewata #Meedorecords #choochoopromotions
5.6K views07:55