ብር ዘገኔ ዕድሜ ማያክላት ዘመን ማይችላት ካንቺ ወዲያ ፥ የተረሳች ማትፈጠር የተዘነጋች ማትቆጠር ማኒቷ ናት ብርዘገኔ ? ሕይወት ነበረች በዚያ ጉራማይሌ የተወቀረች ኹኝ ሲላት ብርዘገን የተባለች ። እሷ ልጅት ፣ ንጽሕት ኮረዳ ፥ ኣፍላ ዝልስ ቀዘባ ሽው እልም እምር ዘንጠፍ ዘና እምትል ወለባ ። ፈክረህ ታውቅ እንደኹ የኑባሬን ኣንድምታ ባክህ ኣንት ኹለንታ ወዲህ ብትላት ፥ ምን ነበር ? መላ እንኳን ብትመታ ። እንዳልችለው ቻል ሲለኝ ውሏን መያዝ ተስኖኝ ( እንደ ረጂም ሌሊት ) ውድቅቷ ዝንታለም ሆኖኝ ቀትሯን ፥ በዳፍንት እየተቀጣኹ ከገዛ ኣንድ ራሴ ፥ እየተጣጣኹ ኣሽቀንጥሮ የጣለኝን ኣስችሎኝ ላልጋደረው በቀት ለጠመደው ፥ ፍጥርጥሬን ላላማርረው በዚህ ግባ በዚህ ውጣ ፣ እያልኩት ላልቃጠረው ቀቢጸን ደቅድቆት ፥ በቁም ሲያቆረቁዘው ሰቀቀን ሆኖኝ ዕድሜ ጉዱ እንዴት ብዬ የዘርፏን ኣንደኛ ጽንፍ ልያዘው ? ኣነበንባለኹ "በቀን ጠሐይ መስኮት" ገጸ - ስጋሽን በኣይነ ህሊናዬን ፥ እስለዋለኹ ። ኣንቺስ ለመሆኑ ኣስተዋልሻት ኣስታወሻት ፣ ያቺን የኔን እናት ሀርሜ ኪይያ ፥ ቢዴና ጠፍጣፊቷን ሽልጦዋን ስገምጠው ማመዛዘን የሚሳነኝን ፥ የገዛ ፈሴን ቅርናት ኣስታወሻት ኣስተዋልሻት መቼም እንዳንቺ መክፋት እንደኔ እንደኔ መጥፋት ቋንቋ ነበርሽ ለሰሞናት ግን ? ኣቻሽ ምኒቷ ናት ። ኣዎ ላንቺ - ለዘመናት ምጤ በእሮሮ ግት ለወለድኩሽ ቀለም ለጠለቅሽኝ ፥ የኪነት ቅምጤ ጣር ነበረ ልቤ እንባ ነበር በእርምጥምጤ ግን ምንሽ ነው የሰረቀኝ ከኣፍላነት ትኩሳቴ ፥ ትኩስ ልምምጤ ? ሕይወት ምርቱን ከግርዱ ላንለየው የወሰደሽን መንገድ ነገር ፥ እህ ብዬ ከኣንድ እራሴ በቀር ለማን ነው ? ለምን ነው ማዋየው ። እንዳልደርስብሽ ርቀሻል እንዳልዳስስሽ ረቀሻል ብቻ ሳስብሽ ሌቱ ይነጋል ሳልምሽ ቀኑ ይመሻል ። እና ምን ይዋጠኝ መድረሻሽን ባወቅኩት ምን ነበር በተከተልኩት እንዲህ እንባ ከመሰለቅ ወይ በየመንገዱ ከምቀር ፥ ወይ በኃሠሣ ከማለቅ ምን ነበር ? ምን ነበር ? ኣንዴ ከዕድሜ ማለዳ ላይ ትኩሳትሽ ከሩቅ ጠርቶኝ የሴት ወጉ ፣ ማዕረጉ ወዳለሽበት ስርፋ መርቶኝ ንፍጤን በቅጡ ሳልጥል ቂጤን በወጉ ሳልጠርግ በየሸጡ ስዳክር ፍጥረትሽን በጨረቋ ቀልቤ ፥ እያማጥኩት ስፈክር ማን ኣየልኝ ? የልቤን ከቀልቤ ሳመሳክር ማን ሰማልኝ ? የኣፌን ከእዝኔ ሳፎካክር ! ኣዎ ቡሃቃ እያገለባበጥኩኝ ጥራጊ ዓለሙን ሳዋስጥ በየመጋዣው ፊንጥጣ ስር ፥ ጉልምስናዬን ሳሯሩጥ ኣለሽበት ስርፋ ከመድረሴ እንደ ልቤ ሳልፋንን ፥ "ቤት ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ" ግን ለስንቱ ኣልሜሽ ማማጤን በየቆቃው ስር ተለጥፌ ፥ ጨለማሽን መለማመጤን ከገዛ ኣንድ ራሴ በቀር ማን አየልኝ? እዚህ ድረስ መርመጥመጤን። ወትሮ መንገድሽን ተከትዬ ስንዝር ላልደርስበት እንደ ዘላን ገላ፣ እንደ መናፍስቱን ፥ ዕድሜ ያልተሰፈረበት ዘሐዓለም ዓለም ነው ፥ ወዲያ ያለሽበት እና በምኔ ልንፏቀቅ እንዴትስ ልጠጋሽ? ልቤን ለጭዳሽ ጣልኩት ጉልበቴን ብጨርሰው ግን.... ግን..... ሞት አውላላውን ሲፎክር፥ የአምላክ ህላዌን ሊካሰሰው መቃብሩ መሀል ቤት - እንደሚምሰው አዎን እንዳመልክሽ ተፈርዶብኛል ልክ እንደገመምተኛ ለው። እንግዲህ እወቂ አንቺን መከተል ደክሞኛል እፎይ ልበል የእረፍት ንሥሀ ያስፈልገኛል። እፎ.....................ይ! አናንያ ተሾመ http://t.me/sufafel 3.0K views17:51